Monday, January 2, 2017

መታደስ ከሆነ ፖለቲኮኞችና ጋዜጦኞች እስረኞች ይፈቱ !!! – ከአስገደ ገብረስላሴ

 አስገደ ገብረስላሴ ፖለቲኮኞችጋዜጦኞች ማሰርሚሊዮኖች ደጋፌዏቻቸው
ጭምር ማሰርና መሳቃዬት ነው !!!
—————————————————
የእነ ደጉተር ምራራ  ጉዴና  በቀለ ገርባ    ሌሎችም የሰላማዊ  ተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዏች አማራርና አባሎቻቸው ማሰሩ  እነሱን ደግፈው እምነት የጣሉባቸው ሚሊዮኖች ኢትዮጱያውያን  ማሰርና መሳቃዬት ብሎም  አስተሳሰባቸው ፣ሰብአዊ ክብራቸው ፣ ነጻነታቸውን  ጭምር መንጠቅ ማለት ነው ።
የሌሎች እንደነ የሰማያዊ  ፓርቲ  ፣ሚኢአድ ፣ ማራርና  ያፈረሱዋቸው የአንድነት  የታሰሩ አመራር  ፣እንዲሁም በትግራይ በእሱር እየተሳቃዩ የሚገኙ የዓረና ባላት ፣ በኃላቸው ሚሊዮኖች ደጋፊዎቻቸው  እንደታሰሩ ይቆጠራል ።
እንደ ተመስገን ደሳለኝ ያሉ እውቅ ጋዜጦኞች  ማሰር ከመድረክ መሰወር ፣ ታሰረው የሀገራችን ህግ የሚፈቅደው የእሱር ጊዚያቸው  ጨርሰው በአመኩሮ እንዳይወጡ  ህገመንግስት መብታቸው መነፈጋቸው ፣
አሞኩሮ መከልከላቸው አልበቃም ብሎ   ተመስገን ደሳለኝ  በታሰረበት ወህን ቤት ወላጅ እናቱ ወንድሞቹ ፣ዘመድ ጓዶኞቹ እንዳይ ጠዩቁት መከልከሉ  የግፍ ግፍ ነው ። ተመስገን ታሞ ተብሎም ቤተሰብ እንዳይ ጠይቁት መደረጉ  ሌላ አሳዛኝ ተግባር ነው ።
እነ ተመስገንና ጓደኞቹ መታሰራቸው  ካገር ተሰደው ለሞት ለሽግር  መዳረጋቸው የነሱ ልሳን ያነበቡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ  ተከታዮቻቸው  እስሮኞች ሆነው የህሊና ስቃይ እየደረሰባቸው ይገኛሉ ።
በመሆኑም ይህ  ስርአት  ለፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና ጋዜጦኞች ብቻ አይደለም አስሮ ያለው ። የነሱ ደጋፌዏች የሆኑ ሚሊዮኖች ኢትዮጱያውያን ጭምር እያሳቃዬ መሆኑ ተገንዝቦ እሱሮኞች  ፈቶ  ከፖለቲኮኞች፣ ጋዜጦኞች ፣በኃላቸው  ከተሰለፉ ሚሊዮኖች  ጋር ታርቆ ለሰላማዊ ታጋዮች ከፍት መድረክ  በመስጠት  መታረቅ አለበት ።  ካለበለዚያ  ለዜጎች  ምክንያት እየፈጠሩ ማሰር መሰቃዬቱ ለዝህች ሀገር አይጠቅማትም ።
የደጉተር ምራራ ገዴና መታሰር ብንመለከት  ወደ አውሮፓ  የጠሩት አውሮፓ ህብረት ናቸው ፣ ለነደጉተር ብርሀኑም ወደመድረኩ የጠሩዋቸው አውሮፓ ህብረት ናቸው ፣ በዛ መድረክ የመንግስት ተወካይ የሆነው አምባሳደር ቶሸመ ቶጋ  ከነቡዱኖቹ  በአውሮፓ ህብረት ተጠርቶ ተሳትፎ ነበር ። ታድያ ደጉተር ምራራ ለብቻቸው በአሸባሪነት ተፈርጀው በወታደራዊ አስተዳደር  እጅ ወድቀው  በስርአቱ ማእከላዊ ምርመራ  መግባታቸው  ለምን ? ደጉተር ምራራ እኮ  ከ1983 ዓ ም ጀምረው የህወሓት ኢህአደግ ተቃዋሚ  ሰላማዊ  ታጋይ ሆነው 25 አመት ለዚህ አንባገነን ስርአት በህጋዊ መንገድ እየተማጎቱ የነሩ ናቸው ። እኔ በአካል አውቃቸው አለሁ   እኔ እንደማውቃቸው   አንድ ቀንም የነውጥና የአመጽ መንገድ ለመራመድ ዝንባለና አስተሳሰብ አለየሁባቸውም  በአንጻሩ  በቁጣ ለሚከራከሩ  ምክርን ይሰጣሉ ። ለደጉተር ምራራ እንደ ድክመት ሊባል ከሆነ በቋንቋ እጥረት ምክንያት  ቃላት አለመምረጥ   ነው ። ይህ ስርአት ደግሞ እችን ደካማ ጎን እያነሳ  ኦሮምኛ ከማይናገር ህዝብ በተለይ ከአማራና ከትግራይ ለመነጠል ቡዙ ጥራል ። ሀቁግን ለደጉተር ምራራ የሚጠላ ኢትዮጱያዊ የለም ።ሌላ ቀርቶ የስርአቱ ካድሬዏች ሳይቀሩ ለምን ታሰሩ እያሉ የሚተቹም አሉ ።
በእኔ እምነት ደጉተሩ ይቅርና በአሸባሪነት ሊፈረጁ የሀገራችን የሰላም ሀርበኛ የሚል ሽልማት  ይገባቸዋል  እእኔ እምለው በአሁኑ ጊዜ ደጉተር ምራራ ሳይሆኑ አሸባሪ አሸባሪ ሆኖ ያለው ራሱ  ይህ  ስርአት  ነው ፣
እኔ እምሰጋው ይህ ስርአት ለአውሮፓ  ህብረት  ፓርላማ  ያለ እነሱ ኢኮኖሚያዊ   ድጋፍ ስለማይኖር ነው እንጅ   አሸባሪዏች ብሎ  ሊያስራቸው የሚያፍር አይመስለኝም ።
ኢህአደግ አመጽ አስነስታችሁ ብሎ  በአስር ሽዏች የሚቆጠሩ ዜጎች በየወታደራዊ ካንፕ  እንደ እንስሳ  አጉሮዋቸው ከርሞ  በውድም ይሁን በግድም ይሁን አይሁን አናውቅም  አንደግምም   በሚል ሞፎከር  ታድሰው እንደወጡ ጠ/ም / ሀይለማርያም ደሳለኝ ነግረውናል ፣ ይህ አባል ህጻን ልጅ  ስህተት ሲፈጽም  ስትቀጣው  ፈርቶ ሁለተኛ አልደግምም  እንደማለት  ይቆጠራል ። እሱሮኞችም ታድሰዋል  ተብለው ሲመረቁ  ክቡር ምኒስትሩ ሲናገሩ ስለ እሳቸው አነጋገር ቡዙ ሰው አፍረዋል ።  እሱሮኞቹ አንደግምም ብለዋል  እጅጉን  ደስብሎኛል ። መንግስትም የፈጸመው ስህተት አይደግም ብለዋል ። ይህ አባባል የዋህነት ይመስለኛል ። መንግስት በትክል ስህተተኛ ካለ ለምን በየወታደራዊ ካንፑ ያሉና ትፈረዳላቹ ተብለው በጽኑ ታስረው ያሉ ወገኖች አይፈቱም?  ለተፈጠረው አመጽና የወደመው ሀብት ተጠያቂው ኢህአደግና እሱ የሚመራው መንግስት ከነመዋቅሩ ነው ፣ብለው ጠ/ ም / ሀይለማርያም ደሳለኝ አሰረግጠው ለኢትዮጱያ ህዝብ ነግረውታል ።  ታድያ መታሰርና መወገድ ያለበት ለችግሩ ጠንቅ የሆነ ኢህአደግ እንጅ ድሀው ህዝብ መሰቃየቱ ለምን ተብሎ  ?
በእኔ እምነት  በሀገራችን ያለው  ችግር በማሰር   ሽብር በመፍጠር አይፈታም ።
አንታደሳለን ብትሉም ሰዏች ብትቀያይሩ ፣ በስብሰባ ብትናጡ  ፣የተጠረጠረ ፣አመጽ ያስነሳ  ፤የፓርት መሪዏች ብታስሩ ፣ጋዜጦኞች ብታከስሙ ፣ ወታደራዊ አዋጅ ብታውጁ ፣ የዲሞክራሲ መርሆዏች  ከመሰረታቸው ካልተፈቱ የህዝብ ተቃውሞ ፈጽሞ አይጠፋም ። በየጦር ካንቦች ታጉረው ያሉ ወገኖቻችንም በሽብርና በጭንቀት አንደግምም ብታሰኙዋቸውም  የዜጎች ፍላጎት በቅንነት  ካልተመለሱ  ፣የሀገራችን ቡሩህ ተስፋ እያጨለማችሁት ናችሁ ።
የህወሓት ኢህአደግ መበስበስ  መቋጫ የለውም ::
——;———–;———–————-/—/———-
:    በ1992  በስብሰናል ተሀድሶ ተብለዋል ፣በ2002 በሰብሰናል እንታደሳለን ተብሎ ነበር ፣ ዘንድሮ 2008 እና 2009 ዓም ተሀድሶ በስብሰናል ብለውናል። ዋዋ ስንት ጊዜ በስብሰናለ ? ብስባሰ ካለ እኮ ጋንግሪን ስለፈጠረ መቆረጥ አለበት ። ኢህአደግ ለ15 አመታት ያህል  በሰበስኩ ብሎ ለ90 ሚሊዮን ህዝብ አጭበርብረዋል ። ስለዚህ  ሰወስት ጊዜ ከበሰበሰ ሁሉም ገላው ጋንግሪን ፈጥሯል በመሆኑ ሸተዋል  አካባቢውም በክሏል  ስለዚህ ምን ይደረግ  ? ፍርዱ  ለ100 ሚሊዮን የኢትዮጱያ ህዝብ ይሁን ።
ሌላ የኢህአደግ ምክርቤት ባለፉት ሁለት ቀናት  ያለፈውን በጥልቀት  የተሀድሶ መድረክ  ሲገመግም  እንደሰነበተና  ተሀድሶው የተሳካ እንደነበረ  ተናግሯል በተለይ ደግሞ  የመድብለ ፓርት ተሳትፎ  እናረጋግጣለን ተቃዋሚዏች ነጻ ሆነው እንዲሰሩ እናደርጋለን ብለዋል ።በተጨማሪም አብረን እንሰራለን  ብለዋል ።
ይህ ስርአት ምን እያለ ነው አብዛኞቹ የሰላም ታጋይ ፓርቲ  መሪዏች  አማራርና አባሎቻቸው  በቅሊንቶ ፣በዝዋይ ፣በሽዋ ሮቢት ፣በቃሊቲ ፣በወታደራዊ ካንፖች ነው ታስረው ያሉ ።ጥቂት ቢኖሩም እንቅስቃሲያቸው  ታግቶ ዛሬ ነገ እንታሰራለን በማለት በዚህ ስርአት ተሸብረውና  ተሸማቅቀው እየኖሩ ያሉ ናቸው ።
ስለዚህ ኢህአደግ ለዚህ  ህዝብ  ባልሆነ ነገር እያንሳፈፈ ከሚያጭበርብረው  እያደረገው ያለው የስልጣኑ እድሜ መራዘምያ ሽርጉድ አቁሞ ከህዝብ ተማክሮ በትክክል ቢታደስ ያሸዋል ። ይህ ስል  ግን ኢህአደግ ጋንግሪን ሆኖ በማይታከምበት ደረጃ ስለደረሰ እስከ ከስልጣን መልቀቅ መሄድ አለበት ።
ኢህአደግ  ከአለም አይማርም እንጅ የሰለጠኑ አገሮች መሪዎች  መምራት ሲያቅታቸው   ፣ህዝብ ሲጠላቸው ራሳቸው ነው በሰላማዊ መንገድ ከስልጣን የሚወርዱ ።
ከአስገደ ገብረስላሴ  መቀለ ፣
24  / 4  /  2009  / ዓ  ም

No comments:

Post a Comment