Friday, January 27, 2017

ይድረስ ለአቶ ገዱ አንዳርጋቸው: ለሆድ ብሎ ገሎ ሊያልፍ ለሚያደባ ጠላት ከመንበርክክ አብሮ ከሚኖረው ህሊና ጥያቄ መንፃትና አኩሪ ህዝብን ይዞ ስምን ተክሎ ማለፍ



ለሆድ ብሎ ገሎ ሊያልፍ ለሚያደባ ጠላት ከመንበርክክ አብሮ ከሚኖረው ህሊና ጥያቄ መንፃትና አኩሪ ህዝብን ይዞ ስምን ተክሎ ማለፍ
ይድረስ ለውድ ወንድማችን አቶ ገዱ አንዳርጋቸው (አንዱ ባለአደራ የአማራ ልጅ)
ወያኔና ግበረ በላዎቹ መገነዣ ልጣቸው ተርሶ መቀበሪያ ጉድጓዳቸው ተምሶ የግብዓተ መሬቱን ስዓት እየጠበቁ እንዳሉ ከእኛ በጓሮ በር ከምንሰልለውና ከምንሰማው ይልቅ አንት በቀጥታ ድንገት አንዳትሰማው ቢፈለግ እንኳ በመላው ጎንደር ምናልባትም አማራ ህዝብ ያለህን ተቀባይነትና የወያኔ መወደቅ አይቀሬ መሆኑን በሚያወቁ አብረውህ በበሉ ሚስጠሩ እንደሚደርስህ እርግጠኞች ነን። አቶ ገዱ አስኪ ቆም ብለህ አስብ? ከአንተ ጀምሮ ዞን ወረዳ መስተዳድሮችህ ስማቸውን አስተካክለው በማይፀፉ የትግሬ አፋኝ ወታደር አዛዞች እዝ ስር ሆነው በቁም አስረኝነት የ10 ሳንቲም ግምት ያለው ትዕዛዝ የማትስጡ አስተዳደራችሁ ፈርሶ ግዑዛን ሰለመሆናችሁና አጣብቂኝ ውስጥ ሰለመሆናችሁ ነጋሪ አትፈልጉም ብለን እንገምታለን።
የብአዴን ምክትል ሊቀመንበርና የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

አንዱ ኢትዮጵያዊ ጅግና ባንድ ወቅት ሁሉም ያመኑዋቸው የማይጠረጥሩዋቸው ሁሉ ከዱዋቸው ከክሃዲዎቹ በእጃቸው የገቡትን ከሳር ጎጆ በማስገባት ሲቃጠሉ ለማየት ከተቀመጡበት ከፍ ካለ ቦታ ሆነው ከሃዲዎቹን ወደ ሳር ጎጆ እንዲያስገባ የመደቡትን ኃላፊ (አሁን አንት በቆምክበት ቦታ የቆመውን ማለት ነው) ሞላ? ብለው ይጠይቁታል እረ አንድ ይቀረዋል በሎ ይመልስላቸዋል ከአንተስ ምን እጠብቃለሁ በል አንተም ግባ ብለው አብሮ ተቃጠለ ይባላል። የአንተም ዕጣ ፈንታ ይህ እንደሆነ ጠንቅቀህ ታውቃለህ “አይጋ ፎረምን ያዩአል”…. ልዩነቱ ይህ ትልቅ ሰው በሀገር ፍቅር ነደው አሁንም ከሰው ያልተሳካላቸውን ድንገት በእሳቱ ተፈትኖ ከአመዱ ሰው ባገኝ አያሉ እያለቀሱ ማድረጋቸው። የአንተዎቹ አለቆች ደግም ለግል ሆዳቸው እንዝረፍ እንደፈለግን እንሁን ሀገር ወገን ገደል ይግባ የሚሉ የሀገርም የወገን ለአገልጋዮቻቸው ለእናንተም ፍቅር የሌላቸው ሆዳሞች መሆናቸው ነው።
አቶ ገዱ ይህ ከእኛ ወገኖችህ የመጀመሪያም የመጨረሻም ምክራችን ነው። እባክህ 37 ሚሊዮን ህዝብ ይዘህ ለ6 ሚሊንም ቢሆን ግጥሚያው አትፍራ? ብትሞት የምትሞተው አንድ ሞት ነው ሞትህ ግን ለልጆችህ አስከ ትውልዳችው ስምህን ከምደር በላይ ዘላዓለማዊ ክብርና ሞገስ ትተህላቸው ከማለፍ ውጭ የምታጣው ነገር የለም። ምክንያቱም እንደ ወያኔ ውሳኔ በእኛ ደጀንነት እንጅ የመኖር ፈቃድህ የእርድ ቀንህን አየጠበቅ እንደሆነ እርገጠኛ ነህ። ይህንም በፍፁም መሰሪነታቸው አንት ልትጠቀምባቸው ትችላለህ ተብለው የሚሰጉ የልዩ ኃይል የማረሚያ ቤቱንና ሌሎች ጀግኖችህን አያሰሩ ቀነዘሉ ተቆርጦ እንደሚደርቅ ዛፍ አጅ አግርህን ክተክተው እየጣሉሀ እንደሁ እንዴት አትረዳም?
በትንሽ መንደሮች በቁጠር አርበኞች ከመላው ኢትዮጵያ የመጣውን ጦር እንዴት እያስተናገድን አየመለስነው እንደሆነ ከምታየው ሰርቶ ማሳያ ብትረዳና እኛ የምንልህን በመቀበል አቋም ይዘህ አምቢ ለአማራ… እምቢ ለኢትዮጰያ… አሻፈረኝ ህዝቤን አትንኩ ተከተለኝ ወገን በማለት ለመሪነት ብትዘጋጅ የምትሳሳላቸውን ቤተሰቦችህን ጨምሮ በአንት ላይ አይደልም ሞት ዝንብ እንደማናሳርፍ መላ ኢትዮጵንም በስዓታት በመድረስ ነፃ እንደምናወጣት ቅንጣት ባትጠራጠርና ስም ብናስር። አትፍራ…. መቸም ሟች ነህ ልዩነቱ በክብር ከመኖር ተስፋ ጋር የክብር ሞት ለመሞት ወይም የተወሰነልህን የማይቀር የወያኔን የውርደት ሞት ለመሞት መዘጋጀት ናቸው።
አንት ባታደርገውም ወያኔ በሚያገኛት ትንሽ ቀን ምናልባት ወራት ወደ እኛ ጎንደሬ አርበኞች የማይነካ አሳት አንድም ትግሬ ሳይጨምሩ አየላኩ እንደማገዶ እንጨት የሚያልቁት ኢትዮጵያዊ ልጆቻችን ሞት አንጅ ወያኔንማ አያክርምን አናከርመውም…።
አሳዛኙ ግን ለእኛ አንት በአድሜህ በትምህርት በባህልም ከእነሱ የተሻለክ ነህ ብለን ስለምንገምት እነዚህ እንጀራ ጠግበው ያልበሉ ሊተኩሱት ቀርቶ ሊሽከሙት የማይችሉትን ጠመንጃ አሸክሞ በርሃብ ለጥይት የሚማግዳቸው ተተኪ ንፁሃን ኢትዮጵያዊ ተባበሪ መሆንህና ወንጀሉን ዝም ብለህ ማየትህ አጅግ እጅግ ያሳዝናል አንተስ ሽክሙን እንዴት ቻልከው?
ስለዚህ ምከረው ምከረው አምቢ ካላ መካራ ይምከረው በሚባለው የአባቶች አባባል ባለብን የደም የስጋ የማንነት ትስስር እራስህን እንደትፈትሽ የከበረ ምክራችን እንለግሳለን መንገዱንም እንዲያሳይህ እንፀልይልሃለን።
ድል ለኢትዮጵያዊያን
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላዓለም ትኑር
መላው ጎንደር አማራ ኢትዮጵያዊያን ንቅናቄ
እባካችሁ ይህ መልዕክት የሚደርሳችሁ ሁሉ በተቻለ መጠን መልዕክቱ ለአቶ ገዱ አንዲደርስ አድርጉልን አናመስግናለን።

No comments:

Post a Comment