Monday, January 30, 2017

ደቡብ ሱዳን ወያኔን ለማስወገድ የትጥቅ ትግል የመረጡ ኋይሎችን መርዳት ከጀመረች የኤርትራ አቋም ይለይለታል። (ቆንጂት ስጦታው)

   


ደቡብ ሱዳን ወያኔን ለማስወገድ የትጥቅ ትግል የመረጡ ኋይሎችን መርዳት ከጀመረች የኤርትራ አቋም ይለይለታል። (ቆንጂት ስጦታው)…………..ይህን ሰሞን መልካም ዜናዎች እየተሰሙ ነው። የደቡብ ሱዳን መሪ ሳልቫ ኬር ድንገተኛ የግብጽ ጉብኝት በወታደራዊ ስምምነት ላይ ጠበቅ ብሎ መታየቱ ግብጽ በደቡብ ሱዳን የኣባይን ወንዝ የሚቀራመቱ ሃገሮችን ተቃዋሚ ሃይላት ወታደራዊ ስልጠና ለመስጠት ማቀዷ ከዩጋንዳው ሙሴቪኒ ጋርም በደረሰች ስምምነት የወያኔ መንግስት ላይ ማሴሯ ኢንዲያን ኦሽን ሌተርና ሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሚዲያዎች ሲነግሩን ከርመዋል።በኤርትራ ውስጥ የሚገኙ እና በተለያዩ ዙሮች እንደተመረቁ የሚነገርላቸው የነጻነት ሃይሎችን ወደ ደቡብ ሱዳን ለማዘዋወር የሚደረገው ስራ ከባድ ፈተና ከሻእቢያ ይገጥመዋል።……..ይህ መልካም ዜና ተከትሎ የሕዝቡ ውይይት በሰፊው እየተሰም ነው። ውይይቱ ያተኮረው ደቡብ ሱዳን ወያኔን ለመጣል የትጥቅ ትግል የመረጡ ሃይሎችን መደርደሪያ መሬት ከፈቀደች ወታደራዊ ስልጣና እንዲያገኙ ካደረገች በኤርትራ ያሉና በተለያየ ጊዜ የተመረቁ የነጻነት ሃይሎች በኣስመራ መልካም ፈቃድ ወደ ደቡብ ሱዳን እንዲሄዱ ይፈቀድላቸው ይሆን የሚሉ ጥያቀዎች እየተነሱ ነው።የኤርትራ መንግስት የነጻነት ታጋዮችን ለመርዳት ከሚሰበሰበው ገንዘብ መካከለኛ የውጪ ምንዛሬ ያገኛል ከወያኔ ጋር የመረጃ ልውውጥ ስላለው ፈቃደኛ አይሆንም እንዲሁም በነጻነት ታጋዮቹ ላይ የጉልበት ብዝበዛ ስለሚያደርግ የተገኘውን እድል ለማክሸፍ ከወያኔ ጋር ተረባርቦ ይሰራል የሚሉ አስተያየቶች እየተሰሙ ነው። ………  በኤርትራ ውስጥ የሚገኙ እና በተለያዩ ዙሮች እንደተመረቁ የሚነገርላቸው የነጻነት ሃይሎችን ወደ ደቡብ ሱዳን ለማዘዋወር የሚደረገው ስራ ከባድ ፈተና ከሻእቢያ ይገጥመዋል።ሻእቢያ የነጻነት ሃይሉ መነገጃ እንዳደረጋቸውና በፍጹም ወደ ጦር ሜዳ እንደማይልካቸው ከላካቸውም መረጃውን ለወያኔ አድርሶ አስከብቦ እንደሚያስመታቸው ከዚህ ቀደም በኤርትራ ቆይተው ጉዳዩን የታዘቡ ሃይሎች ይናገራሉ። በቀጣይነት የሚሆነው እየጠበቅን ለነጻነት ሃይሉ መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን።

No comments:

Post a Comment