Monday, January 30, 2017

ወያኔ የቅማንትን ጉዳይ ‹‹በሪፈረንደም›› መፍትሔ እሰጣለለሁ በማለት ካድሬዎቹን አሰልጠኗል፤ • የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ የሚታሠሩ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል

   


ወያኔ የቅማንትን ጉዳይ ‹‹በሪፈረንደም›› መፍትሔ እሰጣለለሁ በማለት ካድሬዎቹን አሰልጠኗል፤
• የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ የሚታሠሩ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል –
በሰሜን ጎንደር ዞን በጎንደር ዙሪያ፣ በላይ አርማጭሆና አካባቢው ባሉ ወረዳዎች ከቅማንት የማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ሪፈረንደም አካሒዳለሁ የሚለው የወያኔ አገዛዝ ለዚህ ይረዱኛል ያላቸውን ካቢኔዎቹን አሰልጥኖ በዚህ ሳምንት ጨርሷል፡፡ ከዚህ ቀደም ለቅማንት ልዩ ወረዳ ከተካለሉት ቀበሌዎች ውጭ በሆኑ አካባቢዎች ሪፈረንደም እንደሚደረግ የተገለጸ ሲሆን የእርስ በእርስ ግጭት ለመፍጠር የሚደረግ እንቅስቃሴም አለ ተብሏል፡፡ የወልቃይት ጠገዴን የዐማራ ማንነጥ ጥያቄ የትኩረት አቅጣጫ ለማስቀየስ አሁን ሆን ተብሎ የሚጀመረው ሪፈረንደም ወደ ግጭት ሕዝቡ አስቀድሞ ይህን በመገንዘብ አንድነቱን ማሳየት እንዳለበትም መረጃውን ካቀበሉን አካለት አስተያየት ተሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በአዲሱ ዓመት መጀመሪያ መፍትሔ ይሰጠዋል የተባለው የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ ተወላጆችን ትግራይ ክልል ጥያቄ አቅርቡ እያሉ እየላኩ በማሳሰር ጥያቄውን ለማጓተት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ በጠገዴ ወረዳ አካባቢ ያለው የድንበር እና አጠቃላይ የወልቃይት ጠገዴ የዐማራ ማንነት ጥያቄ በሚል በሁለት ተከፍሎ ይፈታል በሚል በነሐሴ ወር 2008 ዓ.ም. በነበረው የኢሕአዴግ ጉባኤ ተቀምጦ ነበር፡፡ በጊዜው የድንበር ጉዳዩ በ15 ቀን እንደሚያልቅ ነበር ለሕዝብ ቃል የተገባው፡፡ በ15 ቀን ያልቃል የተባለው ጉዳይ ግን ከሰባት ወራት በኋላም ዜጎች እየተገደሉና እየታሰሩበት ነው፡፡ የሚከተሉት የወልቃይት ተወላጆች በእስር ከሚገኙት በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

No comments:

Post a Comment