አክሎግ ቢራራ (ዶር)
“ድርጅታዊ ምዝበራ” ብየ የሰየምኩትን መጽሃፍ ስጽፍ ከሁሉም በላይ ያሳሰቡኝና ያስጨነቁኝ አስኳል ጉዳዮች ሶስት ናቸው፤
አንድ፤ አብዛኛው በድህነት፤ በረሃብ፤ በበሽታ፤ በሰብአዊ መብቶት ረገጣ፤ በአስተዳደር ብልሽት የሚሰቃየው ከ90 በመቶ በላይ የሚገመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ አሰቃቂ ደረጃ ላይ መድረሱ ነው።
አክሎግ ቢራራ (ዶር)
ሶስት፤ አንድ ስርዓት በሙስና የተበከለ ከሆነ ሰላምና እርጋታ አይኖርም። በዜጎች መካከል ያለው የገቢና የኑሮ ልዩነት እየተባባሰ ይሄዳል። ይህ አሰቃቂ ሁኔታ ቀስ በቀስ ለአገር መፈራረስ ዋና መንስኤ ይሆናል። ኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስና መዋቅራዊ ሲሆን የሚያስከትለውን አደጋ በመረጃ ተደግፋ ያቀረበችው ደራሲ ሳራህ ቸየዝ “Thieves of State: why corruption threatens global security,” በሚለው መጽሃፏ አፍጋኒስታን፤ ግብጽ፤ ሶሪያ፤ ኢራቅ፤ ናይጀሪያና ሌሎች ተመሳሳይ አገሮች እንዴት በመፈራረስ ላይ እንዳሉ ታሳያለች። ዋናው ነጥቧ የፓርቲና የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ለሕዝብ ያለባቸውን አደራና ሃላፊነት ትተውና ረስተው፤ ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ስላከበሩ አገሮቻቸው የጦርነት አውድማ ሆነዋል የሚል ነው። የሞባረክ መንግሥት የወደቀበት ዋና ምክንያት ሕዝቡን አፍኖ፤ ስልጣኑን ተጠቅሞ፤ ራሱን፤ ቤተሰቦቹን፤ ወዳጆቹንና ደጋፊዎቹን፤ ጀኔራሎቹን ጨምሮ ስላከበረ ነው የሚል ድምዳሜ አቅርባለች። በሙስና የተበከለ አምባገነን መንግሥት የመሳሪያ የበላይነትም ቢኖረው በሕዝብ አመጽ እንደሚወድቅ አሳይታለች። የሙስና አደጋው ለአገር መፈራረስ ግብአት እንደሚሆን መረጃዎችን አቅርባለች።
No comments:
Post a Comment