Saturday, January 28, 2017

የአዲስ አበባ

የአዲስ አበባ- ናዝሬት ፈጣን መንገድ ጥናት የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ መንግስት እቅድ እንደነበረ የዛሬይቱ ኢትዩጵያ ጋዜጣ ቅዳሜ 10 ቀን 1960 ዓ.ም ገጽ 1 እና 3 እንዲህ ያስታዉሰናል፡፡
በሚቀጥሉት 5 ዓመታ ዉስጥ የአዉራ ጎዳና ባለስልጣን የትራፊክ ችግር ለማቅለል ከሚሰራቸዉ የመገናኛ ስራዎች አንዱ የአዲስ አበባ- ናዝሬት ድረስ የሚዘረጋዉ መንታ መንገድ አንዱ ነዉ፡፡ ከአዲስ አበባ- ናዝሬት ድረስ መንገድ በመንታ ለመስራት መታቀዱ ከዚህ በፊትም የተገለጠ ነገር ነዉ፡፡ አሁን እቅዱን በስራ ላይ ለማዋል አስፈላጊ በመሆኑ አሁን የንድፍ ስራዉ በ1960 ዓ.ም ያልቃል፡፡ የቅያሱ ስራ በ1961 ዓ.ም ቀጥሎ የደንበኛ ስራዉን በ1962 ዓ.ም እንዲጀመር ያደርጋል፡፡ አሁን ባለዉ መንገድ ይቀደድ ያልን እንደሆን ብዙ ቤቶች ማፍረስና ግምቱም መስጠት ወጪ የሚያ...በዛ በመሆኑ ሌላ መንታ አዲስ መንገድ መስራት የሚሻል መሆኑን ተረድተናል፡፡
መንግስት አቅሙ ከፈቀደለት መንታ መንገድ በአንድ ጌዜ ይሰራል፤ ግን ለመስራት ካልቻለ አንዱን ሰርቶ ሌላዉን ደግሞ ቦታ ትቶለት ገንዘብ ባለ ጊዜ ሊሰራዉ ይችላል፡፡ አዲስ መንገድ ተሰርቶ በሚያልቅበት ጊዜ መንገዱን ገንዘብ ማስከፈል የሚቻልበት መንገድ አለ፡፡ ይኸዉም አንድ ሰዉ ትራፊክ በማይበዛበትና አደጋ ይደርስብኛል ብሎ ሳይሰጋ ገንዘቡን ከፍሎ እንዲሄድ ይደረጋል፡፡

ክብርና ምስጋና ለእዉነተኛዉ አፍሪካዊ ባለራዕዩ መሪ አባባ ጃንሆይ ቀ.ኃ.ስ
ታሪክ እንዳይነገር ማድረግ ቢቻልም፤ ታሪክ ግን አይሞትም!

No comments:

Post a Comment