Thursday, January 26, 2017

የህወሑት በአዴን አማራር ትጃሮች ከሚለው የቀጠለ — ከአስገደ ገብረስላሴ

ትላንትና ስለትጃሩ የህወሐት አማራር በትግራይ ህዝብ ስም እየነገደ የሚፈጽመው ምዝበራ ከቡዙዏቹ በጥቂቱ ለመግለጽ ሞክሬ አለሁ ፣ ዛሬ ደግሞ የህወሐት ስሪት ስለሆኑ የበአዴን ትጃሮችና ሌሎች በመጠኑም ቢሆን እማውቀው እገልጻለሁ ስለ እምትከታተሉኝ አመሰግናለሁ ።
ቢሊየኖሩ የህወሐት አማራር በትግሉ ጊዜ በተለያዬ መንገድ ያጣራቀመው ብር ፣ዶላር ፣ፓወንድ፣ደችማርክ፣ የሱኡዲ ሩያል ፣ እጅግ ቡዙ ቁሳቁስ ሽጦ ወዘተ ካጣራቀመው ሀብት የኤፈርት ኩባንያዏች ካቋቋመ በኃላ ሁሉም የህወሐት ስሪት ፓርቲዏች በተለይ የበአዴን አማራር በኤፈርት ሀብት የቅናት ምልክት በማንጸባረቃቸው ፣ የህወሐት ትጃሩ አመራር ለአጋር ፓርቲዏች እንደ መስታገሻ ታሳቢ በማድረግ ፣
1 ለበአዴን 60 የተላያዩ መኪኖች ፣ከሞቶ ሚሊዮን በላይ ብርን በመደጎም የአሁኑ የበአዴኑ ትጃር ጥረትን ፣ የአማራ ብድርና ቁጠባ ባንክ እንዲቋቋም አደረገ ።
2 ለኦዴድ አማራር ከ100 ሚሊዮን በላይ ብር እና 35 የጭነት ካሜኖች በመደጎም ድንሾ የሚባል ኩባንያ በማቋቋም የተለያዩ ኩባንያዏች ተቋቁመው ነበር ግን በኦሆዴድ አማራር በሙሱና ተመዘበሩ ። በአሁኑ ጊዜ ምን ደረጃ እንዳሉ መረጃ የለኝም ።
3 የዴሄደን አማራርም በወቅቱ ይቋቋም ስለነበረ እነመለስ ብልጦች ነበሩ እና ደህዴን ጥያቄ ማስነሳቱ አይቀርም ከሚል ታሳቢ በማድረግ ፣ አስቀድመው 70 ሚሊዮን ብርና ከ15 በላይ የጭነት መኪና ተሰጥቶዋቸው ወንዶ የሚባል ኩባንያ እንዲያቋቁም በህወሐት መመሪያ ተሰጥቶዋቸው ተቋቋመ ። ይህ ኩባንያ ቡዙ ሳይራመድ ከስሞ እንደቀረ ነው መረጃውን ያለኝ ።
እንግዲህ የኦሆዴድና የዴሄደን አማራር ኩባኒያዏች እንተዏውና ከህወሐት ትጃሮቹ በ2ኛ ደረጃ የሚሰለፍ የበአዴን ትጃሩ ጥረት እንመልከት ።
የበአዴን አማራር ጥረት ስንትና እነማን የሚባሉ ኩባንያዏች ናቸው ?

No comments:

Post a Comment