Monday, January 30, 2017

ኢትዮጵያ ሰውነታቸውን ባገኙት አጋጣሚ በመሸጥ የሚተዳደሩ ፖለቲከኞች አያስፈልጓትም! ኄኖክ የሺጥላ

ኢትዮጵያ ሰውነታቸውን ባገኙት አጋጣሚ በመሸጥ የሚተዳደሩ ፖለቲከኞች አያስፈልጓትም! ኄኖክ የሺጥላ


ኢትዮጵያ ሰውነታቸውን ባገኙት አጋጣሚ በመሸጥ የሚተዳደሩ ፖለቲከኞች አያስፈልጓትም!
ኤርሚያስ ለገሰ በዋሽንግተን ዲሲ በተደረገው የመፅሃፉ ምረቃው ላይ እነ ሌንጮ ባቲን አመስግኗል። ምክንያት አድርጎ ያቀረበውም « እንዴት እየሄደልህ ነው እያሉ ስለሚጠይቁኝ ነው» ብሏል ። ስለ 11 መፅሃፍ ያነሳው አስቆኛል!
ሰማይ የነካ ቀጣፊነት እና አድርባይነት ማለት ይሄ ነው! በዚህ ችሎታው ነበር የበረከት ስምዖን ሎሌ የነበረው። ኢትዮጵያ እንዲህ ያሉ ሰውነታቸውን ባገኙት አጋጣሚ በመሸጥ የሚተዳደሩ ፖለቲከኞች አያስፈልጓትም! የሚያወሩት ምንም ይሁን ምን የሚያወሩትን የሚያወሩት አምነውበት አይደለም! የፖለቲካ ፍጆታ መሆን የሚችል ፥ የሎሌነት ዘመን ታሪካቸውን መፅሃፍ አድርገው ቢሸጡልን እዳው ገብስ ነው።
እርግጥ አዲስ ማንነትን የወረሱ መስሎን ቀርበናቸው ነበር! ግን ለአዲስ ማንነት ያልተፈጠሩ እንደሆኑ በሂደት በወዳጅነት ዘመናችን ልረዳ ችያለሁ! ከሚሉት ውስጥ አንዱንም አያምኑበትም ! አምታቾች ናቸው! ሰውነትን የነጠፉ ጥርብ ሎሌዎች! እንዲህ ያሉት ሰዎች They are cancerous and an obstacle for the creation of a free spirited generation !
ኄኖክ የሺጥላ

No comments:

Post a Comment