Monday, January 23, 2017

ለተከሰተው አመፅና አለመረጋጋት ዋናው ተጠያቂ አንድ ሰው ነው – ስዩም ተሾመ

   


ለተከሰተው አመፅና አለመረጋጋት ዋናው ተጠያቂ አንድ ሰው ነው – ስዩም ተሾመ
ካለፈው ዓመት ጀምሮ በሀገራችን የታየውን አመፅና አለመረጋጋት በማነሳሳት ረገድ ተጠያቂ ናቸው የሚባሉት አካላት ብዙ ናቸው። ግብፅና ኤርትራ፣ ኦነግና ግንቦት7፣ የኒዮሊብራል አራማጆች እና የቀለም-አብዮት አቀንቃኞች፣…ወዘተ። ከእነዚህ ውስጥ እኔ በየትኛው እንደምመደብ ባላውቅም “ሕዝብን ለአመፅ በማነሳሳት” በሚል ወንጀል ተከስሼ ለ82 ቀናት ያህል በእስር ቤት እና በተሃድሶ ስልጠና ላይ ቆይቼያለሁ። በጦላይ በተሰጠኝ የተሃድሶ ስልጠና መሰረት አንድ የተገነዘብኩት ነገር ቢኖር ከላይ ከተጠቀሱት ኃይሎች ለተከሰተው አመፅና አለመረጋጋት የነበራቸው ሚና አንድ ላይ ቢደመር እንኳን ከአንድ ግለሰብ ሚና እንደማይበልጥ ነው። ለመሆኑ በዋናነት ተጠያቂ የሆኑት እኚህ ግለሰብ ማን ናቸው፣ ለምንና እንዴት?
በጦላይ የሚሰጠው የተሃድሶ ስልጠና በዶክመንተሪ ፊልሞች እና በዜና ዘገባ ጥንቅሮች የተደገፈ ነበር። ማታ ከ2፡00 በኃላ ሰልጣኞች/እስረኞች ከመኝታ ክፍሎቻችን አቅራቢያ በሚገኝ ሜዳ ላይ እንቀመጥና የተዘጋጁትን ቪዲዮዎች በፕሮጀክተር እንመለከታለን። ከእነዚህ ውስጥ እንቅልፍ ሳይወስደኝ በንቃት የተከታተልኩት ዶክመንተሪ የቀድሞ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በ1995 ዓ.ም በሀገራዊ ፖሊሲ ዙሪያ ለከፍተኛ አመራሮች የሰጡትን ስልጠና ነው። ከዚያ በፊት በተደጋጋሚ ተመልክቼዋለሁ። ነገር ግን፣ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር አያይዤ በጥልቀት ለመመልከት እድልና ግዜ አልነበረኝም።
በተጠቀሰው ወቅት ጠ/ሚኒስትሩ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደነበሩ በግልፅ ያስታውቃል። በተደጋጋሚ በሚከሰተው ድርቅና ረሃብ፣ እንዲሁም ዝቅተኛ በሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ሲጨመርበት ድህነት በሀገሪቱ ላይ የሕልውና አደጋ እንደጋረጠ ተገንዝበዋል። ጠ/ሚኒስትሩም በወቅቱ ለገጠማቸው ችግር መፍትሄ ለመሻት ብዙ ዘመናት ወደኋላ ተጉዘው የህዝቡን ኑሮና አኗኗር እንደገና ለማጤን ተገደዋል። አቶ መለስ የተናገሩትን ቃል-በቃል ለማስታወስ ቢከብደኝም ዋና ፍሬ ሃሳቡን ግን እንደሚከተለው ለማስቀመጥ እሞክራለሁ፡-
“ለብዙ ዘመናት በተራራዎች ተከበን፣ ከሌላው ዓለም ተነጥለን በድህነት ውስጥ ስንኖር ነበር። በድሮ ግዜ በድህነት ውስጥ በዘላቂነት (sustainably) መኖር ይቻል ነበር። አሁን እየጨመረ ካለው የሕዝብ ቁጥር አንፃር፣ በድህነት ውስጥ እንኳን እንደ ድሮ መኖር የማንችልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። ስለዚህ ፈጣንና ተከታታይ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ የሕልውና ጉዳይ ነው። …ልክ እንደ ድህነት የመልካም አስተዳደር ችግርም ለኢትዮጲያ ሕዝብ አዲስ ነገር አይደለም። ከዚያ ይልቅ፣ ለሕዝቡ አዲስ ሊሆን የሚችለው መልካም አስተዳደር ራሱ ነው…”
በዚህ መልኩ ለሀገሪቱ ክፍተኛ አመራሮች በሰጡት ስልጠናና አመራር ከ1995 ዓ.ም በኋላ ባሉት አስር አመታት ሀገሪቱ ፈጣንና ተከታታይ የሆነ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብ በቃች። ከመሰረተ ልማት ግንባታ ጋር በተያያዘ በመንገድ፣ ትምህርት፣ የኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እምርታ ሊባል የሚችል ለውጥ ተመዘገበ።
የቀድሞ ጠ/ሚ አቋም በጥቅሉ ሲታይ፣ ፈጣንና ተከታታይ የሆነ የኢኮኖሚ እድገት በማስመዝገብ ድህነትን መዋጋትና መቀነስ ካልተቻለ በስተቀር ሀገሪቱ የመበታተን አደጋ ያጋጥማታል።…ለኢኮኖሚ እድገት ቀጥተኛ የሆነ አስተዋፅዖ ባይኖረውም፣ ዴሞክራሲ በራሱ ጠቃሚና አስፈላጊ ነው ብለው ያምናሉ። እዚህ ጋር አቶ መለስና ተከታዮቻቸው ፈጣንና ተከታታይ የሆነ የኢኮኖሚ እድገት የመልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ጥያቄን ከቀን ወደ ቀን እንዲጨምር እንደሚያደርገው በደንብ የተገነዘቡት አይመስለኝም። የእሳቸውን ሌጋሲ እናስቀጥላለን ከሚሉት ውስጥም አብዛኞቹ ይህን እውነታ በግልፅ የተገነዘቡት አይመስለኝም።
በእርግጥ አንዳንድ የኢህአዴግ ባለስልጣናት በሀገሪቱ እየታየ ላለው የሕዝብ አመፅና ተቃውሞ መንስዔው ሀገሪቱ ላለፉት 25 ዓመታት እያስመዘገበችው ልማትና እድገት እንደሆነ ሲናገሩ ይሰማል። ነገር ግን፣ ልማትና እድገት እንዴት ለአመፅና አለመረጋጋት መንስዔ እንደሚሆን የጠራ ግንዛቤ ያላቸው አይመስለኝም። ፅንሰ-ሃሳቡን በግልፅ ለመረዳት በቅድሚያ በልማትና እድገት እና በዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ችግር መካከል ያለውን ቁርኝት በዝርዝር መረዳት ያስፈልጋል።
ልማትን “ሰላም፥ ጤና፥ ትምህርት እና የመሰረተ ልማት መስፋፋት” በማለት በአጭሩ መግለፅ ይቻላል። እነዚህ አራት መሰረታዊ ነገሮች የዳበረ ማህበራዊ ግንኙነት እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲኖር በማስቻል የዜጎችን ኑሮና አኗኗር እንዲሻሻል ያስችላሉ፣ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ያደርጋሉ። ስለዚህ፣ ልማት ከቦታና ግዜ አንፃር የዜጎችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ፈጣንና ቀልጣፋ ያደርጋል። “ፖለቲካ” ደግሞ የሕዝቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ግንኙነት የሚመራበት ሥርዓት ነው። ስለዚህ፣ ፈጣን የሆነ እድገትና ልማት ማስመዝገብ ፖለቲካዊ ስርዓት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሻሻል ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው። በዚህ መሰረት፣ በአንድ ሀገር ውስጥ ልማትና እድገት እስካለ ድረስ ሀገሪቱ የምትመራበት የፖለቲካ ስርዓት ከቀን ወደ ቀን እየተሻሻለ መሄድ አለበት።
በመሰረቱ፣ ማንኛውም የልማት ስራ ዓላማው ብዙኑን የሕብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረግ ነው። ምክንያቱም፣ በአንድ ሀገር ውስጥ ልማት ሊኖር የሚችለው በብዙሃኑ የሕብረተሰብ ክፍል ዘንድ ሰላምና ደህንነት ሲኖር፤ የጤና፥ ትምህርትና ሌሎች ተቋማት አገልግሎት ተደራሽ ሲሆኑ፤ የመንገድ፣ ውሃ፥ መብራት፥ ቴሌኮምዩኒኬሽን መሰረተ-ልማት አውታሮች ሽፋን ሲጨምር ነው። ስለዚህ፣ ልማት ብዙሃኑን የሕብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ በማድረግ እኩልነት (equality) እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ያስችላል።
የልማት መሰረታዊ ዓላማ አብዛኛውን የሕብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረግ ነው። እኩልነትን ለማረጋገጥ በቅድሚያ በዜጎች መካከል ያለው ልዩነት (Inequality) መጋለጥና መታወቅ አለበት። በዚህ መሰረት፣ የልማት የመጀመሪያው ግብ ደግሞ በተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ያለው ልዩነት ማጋለጥ ነው። ይህ የልማቱ አካል በሆኑት የመገናኛና ኮሚዩኒኬሽን አውታሮች አማካኝነት የሚከናወን ይሆናል። በዚህ መልኩ፣ ልማት የእኩልነት እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄን ያስከትላል። ልማት የዴሞክራሲ ጥያቄን ይወልዳል።
በሀገራችን ከ1995 ዓ.ም ጀምሮ የተመዘገበው ፈጣን እድገት በዜጎች መካከል ያለውን የገቢ ልዩነት አስፍቶታል። በተለይ በመንገድ፣ ትምህርትና በኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ረገድ የተመዘገበው ፈጣን የሆነ የመሰረተ ልማት መስፋፋት በዜጎች መካከል ያለውን የመረጃ ፍሰት በብዙ እጥፍ አሳድጎታል። ይህ በገጠርና በትናንሽ ከተሞች የሚኖሩት ወጣቶችን በውጪና በሀገር ውስጥ በሚገኙ ትላልቅ ከተሞች ያለውን የተቀናጣ ኑሮና አኗኗር በቀላሉ እንዲያውቁ ያስችላቸዋል። በገጠርና በትናንሽ ከተሞች የሚገኙ ወጣቶች በኑሮና አኗኗር ደረጃ ቀድሞ የነበረውና አሁን እየተፈጠረ ስላለው ልዩነት ግንዛቤ ተፈጥሯል። ይህን ተከትሎ በተለይ በልማቱ እኩል ተጠቃሚ ባልሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ የእኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄ ተነስቷል። ከእነዚህ የሕብረተሰብ ክፍሎች የሚነሱ ጥያቄዎች በሂደት ወደ አመፅና ተቃውሞ እየተቀየሩ ለግጭትና አለመረጋጋት ምክንያት ይሆናሉ።
በአጠቃላይ ሀገራት ፈጣን የሆነ ልማትና እድገት ማስመዝገብ ሲጀምሩ ግጭቶችና አለመረጋጋቶች በብዙ እጥፍ ይጨምራሉ። ለምሳሌ ቻይና ፈጣን የሆነ የኢኮኖሚ እድገት ባስመዘገበችባቸው አስር ዓመታት ውስጥ የአመፅና አለመረጋጋት አደጋዎች ከአስር ሺህ ወደ ስልሳ ሺህ ጨምሯል። ይህ በሀገራችን በተጨባጭ እየታየ ከመሆኑ በተጨማሪ፣ እንደ ቻይናና ህንድ ባሉ ሀገራት ጭምር በተግባር የተረጋገጠ ክስተት ስለመሆኑ የዘርፉ ተመራማሪዎች ከነምክንያቱ እንዲህ ሲሉ ይገልፃሉ፡-

No comments:

Post a Comment