Monday, January 30, 2017

በቅማንትና አማራ ስም ህዝብ ለማፋጀት አዲስ እቅድ ወጣ! ሕዝብ ይወቀው! ከፍተኛ ጥንቃቄ!


   

በቅማንትና አማራ ስም ህዝብ ለማፋጀት አዲስ እቅድ ወጣ!
ሕዝብ ይወቀው! Must Share! ከፍተኛ ጥንቃቄ!
የሰሜን ጎንደርን ህዝብ በቅማንት እና አማራ የማይገቡ ወረዳና ቀበሌዎችን በማካለል የውሸት ሪፈረደምን ተግባራዊ በማድረግ የእርስ በርስ ጦርነት እንዲያደርጉ እና እነሱም ጣልቃ በመግባት የሚፈልጉትን በግላጭ ለመግደልና ለማሰቃየት እኩይ ተግባሩን በቀላሉ ለማሳለጥ የሚያስችሉ ካድሬዎቹን አሰልጥኖ ስራ አስጀምሯል፡፡ ወያኔ የሚያደርገውን ደም አፋሳሽ አዲስና ተጨማሪ ክለላ ህዝቡ ሆን ተብሎ እንደተቀነባበረ ሊያውቅና እንደበፊት ቀደሙ በከፍተኛ ብልሃት እንዲያልፉት የሚፈጠረውን ችግር እንዲያመክን መልእክቱ በአስቸኳይ ለሁሉም እንዲዳረስ ይሁን።
ይህንን መሰሉን መሰሪ የወያኔ መርዛማ እቅድ ለማሳካት ዛሬ የሰሜን ጎንደር ዞን የፀጥታ አመራሮች ሁሉም ደባርቅ ነበሩ። የፀጥታ አመራሮች፣ የፖሊስና የልዩኃይል ኃላፊዎች አስቸኳይ ስብሰባ ማድረጋቸው ታውቋል።
ከሁለት አመት በፊት ጀምሮ ወያኔ የወልቃይት ጥያቄ በተለይ ጎልቶ ሲመጣበት በፍቅርና በአንድነት የሚኖረውን የጎንደርን ሕዝብ እርስ በእርስ ለማፋጀት የቅማንትና የአማራ በሚል ትልቅ አደጋ ማድረሱ ይታወቃል። ይህን መሰሪ ተግባር የጎንደር ህዝብ አንከፋፈልም በማለት ጠንካራ ምላሽ ቢሰጥም ወያኔ በዚህ መርዛማ ተግባሩ ሊቀጥል መወሰኑን በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል። በቅርቡ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. የወያኔ ኢምባሲ ለሰበሰቧቸው ካድሬወች ጎንደር ያለውን ከባድ ህዝባዊ ትግል ለማክሸፍ የአማራና የቅማንት አጀንዳን ዳግም እንደሚቀሰቅሱት መረጃው ደርሶን አጋልጠናል።
ሙሉነህ ዮሃንስ

No comments:

Post a Comment