Tuesday, January 24, 2017

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የተራበው ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ነው – ዘነበ ዘ ቂርቆስ

የወያኔ ስርዓት ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ ጀምሮ ከ5 ያላነሱ ከባድ ርሃቦች ተከስተዋል ሆኖም ግን በባባሪያ አሳዳሪዎቻቸው ምዕራባውያን ከለላ ምክንያት እስከ ዛሬ ገበናቸው እየተሸፈነ ቆይቷል ሆኖም ግን ከጊዜ ወደ እየባሰበት እንጂ እየተሻሻለ መምጣት ያቃተው የረሃብ ጉዳይ ለተከታታይ ሁለተኛ ዓመት ዘንድሮ በድጋሚ በምስራቅ በምዕራብ እና አንዳንድ የሰሜኑ ክፍሎች የርሃብተኛው ቁጥር እየጨመረ ይገኛል በተለይ በምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል ኦጋዴን አካባቢ ከፍተኛ ከፍተኛ የሆነ የረሃብ አደጋ አንዣቧል ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የረሃቡን አደጋ ከወዲሁ ለመከላከል በአገሪቷ ያለው የአስቸኳይጊዜ አዋጁ እንቅፋት እየሆነ እንዳለና ተረጂዎች በጊዜው እርዳታ ለማግኘት ባለመቻላቸው ምክንያት ለከፍተኛ የጤና መቃወስና ለሞት አደጋ ተጋልጠው ይገኛሉ ። አንዳንዶቹም አቅም ያላቸው አካባቢያቸውንና ቄያቸውን ለቀው ለመውጣት ቢሞክሩም አሁን በአገሪቷ ያለው ወታደራዊ አገዛዝ አካባቢውን ለቆ መሄድ ማንኛውንም እርምጃ ሊያስወስድ በመቻሉ ይህንን በመፍራት ባሉበት እንዲቀሩ ሆነዋል ።
በተለይ በዚህ በኦጋዴን አካባቢ ያለው አስተዳደር በደል ከሁሉ የከፋ እንደሆነና በቅርቡ እንደምናስታውሰው የሱማሌው ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሃመድ ኦማር የክልሉን በጀት ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ለትግራይ ህዝብ መልሶ ማቋቋሚያ በሚል ያለ ህዝብ ፈቃድ አውጥተው ለባሪያ አሳዳሪዎቻቸው መስጠቱ አይዘነጋም ።
ዋይ ዋይ ሲሉ የረሃብን ጉንፋን ሲስሉ
ዘነበ ዘ ቂርቆስ


 

No comments:

Post a Comment