Thursday, January 12, 2017

ሰሜን ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ ግንባር ከትግራይ የተነሳ ሃይል ተደመሰሰ | 16 ሙቶ ብዙ ቆሰለ | ገዱ አንዳርጋቸው በወታደሮች ታጅቦ ደባርቅ ይገኛል

የሙሉነህ ዮሐንስ ዘገባ
ከትግራይ በሽራሮ በኩል ተከዜን ተሻግሮ ወደ ወልቃይት ጠገዴ ይጓዝ የነበረውን የወያኔ ወታደራዊ ኮንቮይ አድፍጠው የቆዩ የአካባቢው ጀግኖች ከፋኞች ድባቅ መተውታል። እጅግ የሚያስደስተው ደግሞ ወያኔ ይጠቅሙኛል ብሎ ያሰባቸው ያካባቢ ሚሊሺያ ታጣቂወች ከህዝቡ ጋር አብረው ተሰልፈው የወያኔ ሃይል መውጫ እንዳያገኝ አድርገው ቀጥተውታል።
በደረሰን መረጃ መሰረት 16 ወያኔ ተገሎ ወደ 30 ሲቆስል ብዛት ያለው ቀላልና የቡድን መሳሪያወች ተማርከዋል። ሰፊውን የሁመራ ወልቃይት ጥገዴና ጠለምት መሬቶች በገፈፋ ከጎንደር የነጠቀው ወያኔ አሁንም እንደ ግጨው የመሰሉ ሰፋፊ የጠገዴ ተጨማሪ ቦታወችን ወደትግራይ ለመውሰድ ከመሞከር አልቦዘኑም። ተከዜን ተሻግረው ካልሄዱ ጤናም የለ እረፍትም የለ! ጎንደር ወስኗል! አማራ ወስኗል! ኢትዮጵያም ወደ ቀደም ክብሯ ትመለሳለች::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ የአማራ ክልል ር ዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ሰሜን ደባርቅ ከተማ እንደሚገኝ ታወቀ:: ዛሬውኑ ዳባት ደርሶ ወደጎንደር እንደሚመለስ መረጃ አለ::

ፎቶው ያጀቡትን ዘመናዊ መኪኖችና የወታደር ጋጋታ ያሳያል። የፈሪ ዱላ! የምንትስ ባል ከሞት አያስጥል! ለልምምጥ የሄደው ገዱ የህዝብን ጥያቄ መመለስ አይችልም።
የጎንደር ሕዝብ ላይ አለቆቹ ወያኔዎች ሙሉ ጦርነት ሲከፍቱበት ከአሽከርነት የላቀ ድርሻ የሌለው የበድኑ የብአዴን መሪ ገዱ ሰልፉን እንዲያስተካክል ያገኘውን አጋጣሚ ሁሉ አሟጦ እየጨረሰ ነው። ወያኔም ጉርቦውን ልትፈጠርቀው አድብታ እየጠበቀች ነው።
ወያኔን በቅጡ የተረዷትና የቀደሟት የተከፉ የጎንደር ጎበዝ አለቆች ናቸው! ሰሞኑን ቆላማውን የወገራ ህዝብ ከጎበዝ አለቆች ጋር አሸማግሉኝ ምህረት ይጠይቁ እያለች ከንቱ ልፋት ላይ ነች።
የነፃነት ጥያቄ በአፈና አይመለስም!
ህዝብ ያሸንፋል©!

No comments:

Post a Comment