Wednesday, September 21, 2016

የኢሬቻ ባህል በዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስ ተብሎ ሊመዘገብ ነው ተባለ



የዘንድሮው የኢሬቻ በአል በመስከረም 22 ሲከበር አመታዊ በአሉ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት የባህልና የሣይንስ ማዕከል ዩኔስኮ በአለም ቅርስነት ይመዘገባል ተባለ…ሸገር ወሬውን የሰማው ከአባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ሮቢ የቱለማ አባ ገዳና የኦሮሚያ አባገዳዎች ሰብሣቢ ነው፡፡
የኦሮሞ የገዳ ስርአት በማይዳሰስ ቅርስነት ዘንድሮ ኢሬቻን ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ የአባ ገዳዎቹ ሰብሣቢ ነግረውናል፡፡ ከወራት በፊት በኦሮሞ የገዳ ስርአት የሚከበረው የኢሬቻ በአልን በተመለከተ የመንግሥታቱ ድርጅት ከዩኔስኮ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል ያሉት አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ሮቢ ከቀናት በኋላ የሚከበረው የኢሬቻ በአል በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት ይመዘገባል የሚል ሙሉ እምነት አለን ብለዋል፡፡
የኢሬቻ በአል በየአመቱ መስከረም 22 ቀን በታላቅ ድምቀት በቢሾፍቱ ሲከበር በርካታ አመታትን ማስቆጠሩ ይታወቃል፡፡

No comments:

Post a Comment