Wednesday, September 21, 2016

ንግሥት ይርጋ፤ የአማራ ተጋድሎ ትዕምርት! ወሮበላው ወያኔ በአዲሱ የአማራ ትውልድ አይበገሬነት ግራ ተጋብቷል፡፡


ንግሥት ይርጋ፤ የአማራ ተጋድሎ ትዕምርት!
Image may contain: horse, one or more people and outdoor
ወሮበላው ወያኔ በአዲሱ የአማራ ትውልድ አይበገሬነት ግራ ተጋብቷል፡፡ አማራን በመጨፍጨፍ፣ ልጆቻችን በገፍ በማሰር፣ በማሰቃየትና በማሳደድ የሕዝባችን አንገት ለማስደፋት እንዳበደ ውሻ እየተናከሰ ቢሆንም፣ በየዕለቱ እየተዋረደ ነው፡፡ የዚህን ርካሽ ፋሽስታዊ ቡድን ጸረ አማራ ተግባር በመደገፍ፣ አማራ ክልል ውስጥ የሚኖሩ በርካታ ትግሬዎችና የወያኔ ጉዳይ አስፈጻሚ የሆኑ ባንዳዎች በሕዝባችን ላይ የታወጀው የዘር ማጥፋት ጦርነት ተዋናዮች መሆናቸውን ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ የሆነ ሆኖ፣ ወያኔና ተላላኪዎቹ የቱንም ያህል ቢገድሉንና ቢያስሩን፣ ከዚህ በኋላ የአማራን ሕዝብ አንገት ማስደፋት ከቶ አይቻላቸውም!!
በየዕለቱ በሕዝባችን ላይ የሚፈጽሙት ዘግናኝ የዘር ማጥፋት እርምጃ፣ ይበልጥ ደም እያቃባንና ይበልጥ የወንድሞቻችና እህቶቻችን ደም ለመመለስ ኃይል እየሆነን ይሔዳል እንጂ፣ ከዚህ በኋላ ከጠላቶቻችን ጋር ምንም ዓይነት ኅብረት አይኖረንም፡፡ ወይ ያጠፉናል፤ ወይ እናጠፋቸውና ህልውናችን እናስጠብቃለን፡፡ ሌላ ምርጫ የለም፡፡ አማራ ደሙን መመለስ ይችልበታል!! የልጆቻችን ደም እጥፍ ድርብ ሆኖ ይመለሳል!!
አዲሱ የአማራ ትውልድ አይበገሬነትና ጽናት ያንገበገበው ወያኔ፣ ይህን የማይቀለበስ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ለማኮላሸት፣ የአማራ ተጋድሎ ትዕምርት የሆነችውን ንግሥት ይርጋን አፍኖ ማዕከላዊ ወስዷታል፡፡ ወያኔ ነገሩ ሁሉ እንደጠፋበትና እንደተሸነፈ ግልጽ የሚሆንልን እንደ ንግሥት ይርጋ ያሉ የትውልዱን ምልክቶች በማሰር ትግሉን አዳክመዋለሁ ብሎ ስትራቴጂክ ስህተት ሲፈጽም ስንታዘብ ነው፡፡ ጀግናው የአማራ ልጅ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እስር ቤት ነው የሚገኘው፤ ሆኖም የትግሉ ምልክት እሱ ነው፡፡ ጀግኖቹ የወልቃይት ኮሚቴ አባላት እስር ቤት ነው ያሉት፤ ነገር ግን የትግሉ መንፈሶች እነሱ ናቸው፡፡ ንግሥትም ማዕከላዊ ገብታለች፤ ሆኖም የተጋድሎው ትዕምርት እሷ ናት፡፡
ምልክቶቻችን ታሰረው እረፍት የሚባል ነገር አይኖረንም፡፡ ጀግኖቻችን ሳይፈቱ፣ ሕዝባችን ነጻ ሳይወጣ፣ ደማችን ሳንመልስ አንተኛም! አናርፍም! ጠላቶቻችን በምንችለው ሁሉ የትም ሆነን እንታገላቸዋለን! እንበቀላቸዋለን! ሚሊዮን ደመቀ ዘውዱዎች፣ ሚሊዮን ንግሥት ይርጋዎች አሉን፡፡ ብዙ ነን! ተሰባስበናል!

No comments:

Post a Comment