Thursday, September 22, 2016

ማዕከላዊ በእስር ላይ የሚገኘው ስንታየሁ ቸኮል ለጥቅምት 10 ተቀጠረ


ስንታየሁ ቸኮል ለጥቅምት 10 ተቀጠረ
በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል (ማዕከላዊ) በእስር ላይ የሚገኘው ስንታየሁ ቸኮል ለሁለተኛ ጊዜ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀበት።
ስንታየሁ ቸኮል ዛሬ መስከረም 12 2009 ዓ.ም በአራዳ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የቀረበ ሲሆን ፖሊስ ምርመራዬን አልጨረስኩም ብሎ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቆበታል። ፍ/ቤቱ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮውን በመፍቀድ ተለዋጭ ቀጠሮ ለጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም ሰጥቷል።
ስንታየሁ ቸኮል፣ የታሰረበት ክፍል ውስጥ እንዲፀዳዳ እየተደረገ እንዳለ ለፍ/ቤቱ አቤቱታውን ማሰማቱን ለማወቅ ተችሏል።
ስንታየሁ ቸኮል ከነሐሴ 14 ቀን 2008 ዓ ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment