Saturday, February 11, 2017

ከአሜሪካ ለኢንቨስትመንት የመጡት ከፍተኛ ግፍ ተፈፀመባቼው!


( ለጥንቅሩ የጎህ ጋዜጠኛ ዞብል ነኝ)
ከጎንደር
ከጎንደር ከተማ ታፍሰው ባለፈው ወራት ብርሸለቆ ታሰረው ከነበሩት መካከል የተወሰኑ የተፈቱ እንዳለ ሆኖ ፣ በርካታ ቁጥር ያላቼው ግን እሰከ ዛሬ ድረስ ያልተፈቱ እንዳሉ ይታወቃል።
አንድ አሳዛኝ ዜና ከወደ ብር ሼለቆ አገኜሁ መላው አለም ይሰማው ዘንድ እንዲህ ዘገብኩት ፣ ከኢትዮጵያ ተሰደው 25 ዓመት በአሜሪካ የኖሩ እና ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ በሀገሬ ኢንበስት አድርጌ እራሴንም ወገኔንም እጠቅማለሁ ብለው በማሰብ በ ጠገዴ ወረዳ በእርሻ ስራ ተሰማርተው የሚገኙት በለሃብት የጠገዴ ተወላጅእና በእድሜ የገፉ ማለትም የ60 ዓመቱ አዛውንት አሁን በወያኔ ማጎሪያ በብርሼለቆ ከሌሎችም የከፋ ከባድ ስቃይ እየደረስባቸው እንዳለና ማንም ጠያቂ እንዳይጎበኛቸው መደረጉን የውስጥ መረጃዎች አጋልጠዋል። ጎንደሬነት ወንጄል በሆነበት በዚህ ዘመን ጎንደር በህዋህት ታፍኖ እየተቀጠቀጠ ይገኛል።

በተያያዘ ዜና በሰሜን ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ የአብራጅራ የኮርሁመር የግራ ውሃ የአብደራፊ የዘመነ መሪቅ የመጎሴ ቀበሌ ኑዋሪዎች መኖራቸውን እየለቀቁ መሆኑ ታውቋል ።
መኖራቸውን ለቀው እንዲሄዱ ምክንያት የሆናቸው በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም ባለመኖሩ ሲሆን የተለመደው የንግድ እንቅስቃሴም ዜሮ ላይ መድረሱን ከአካባቢው የተገኘው መረጃ አመልክተዋል

No comments:

Post a Comment