Sunday, February 26, 2017

የቀድሞው የጋምቢያ ፕሬዚዳንት የዘረፉት ገንዘብ 1 ቢ. ዶላር ደርሷል

    



በምርጫ ቢሸነፉም ስልጣኔን አልለቅም ብለው ለሳምንታት ካንገራገሩ በኋላ በተደረገባቸው ጫና አገራቸውን ጥለው የተሰደዱት የቀድሞው የጋምቢያ ፕሬዚዳንት ያያ ጃሜህ ከአገሪቱ ካዘና ያለአግባብ የዘረፉት ገንዘብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያህል መድረሱን አዲሱ የአገሪቱ መንግስት አስታወቀ፡፡
አዲሱ የአዳማ ባሮው መንግስት ሚኒስትሮች ያወጡትም መረጃ ጠቅሶ ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው፣ ተሰናባቹ ያያ ጃሜህ ከተለያዩ የአገሪቱ የመንግስት ተቋማት በየሰበብ አስባቡ ያለ አግባብ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉት ገንዘብ በድምሩ 1 ቢሊዮን ዶላር ያህል መድረሱ በምርመራ ተረጋግጧል፡፡
ጃሜህ ከማህበራዊ ዋስትና፣ ከስፖርት እና ከቴሌኮም ድርጅቶች ብቻ 50 ሚሊዮን ዶላር ዘርፈዋል፤ ለግል አውሮፕላናቸው ግዢ ያለ አግባብ ከመንግስት ካዘና 4.5 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ተደርጓል፣ እጅግ በርካታ ገንዘብም ያለ አግባብ ለግል ጥቅማቸው እንዲውል ተደርጓል ብሏል ዘገባው፡፡
ከአገሪቱ የማህበራዊ ዋስትና ካዘና ወጪ የተደረገ 40 ሚሊዮን ዶላር ያህል ገንዘብ የት እንደገባ አለመታወቁን የጠቆመው ዘገባው፣ ገንዘቡ በጃሜህ ኪስ ውስጥ ሳይገባ አይቀርም ተብሎ መጠርጠሩንና ቅንጦት ወዳጁ ጃሜህ በየሰበብ አስባቡ ደጋፊዎቻቸውን ለማስደሰት ባደረጓቸው የእራት ግብዣዎችና የቅንጦት ተግባራት 67 ሺህ ዶላር ያህል ወጪ መደረጉም ተነግሯል፡፡
ይሄም ሆኖ ግን ተመድ ለተጠቀሱት አራት አገራት የሚያስፈልገውን 4.4 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ያደረገው ጥረት ይህ ነው የሚባል ውጤት አለማግኘቱንና እስካሁን ድረስ ማግኘት የቻለው 90 ሚሊዮን ዶላር ያህል ብቻ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ጸሃፊው፣ አለማቀፉ ማህበረስብ በአፋጣኝ የድጋፍ እጁን እንዲዘረጋ ጠይቀዋል፡፡

No comments:

Post a Comment