Thursday, February 16, 2017

ሀወሐት በ42 አመት በትግልና በስልጣን አገዛዙ ዘመን ለትግራይ ህዝብ ብለው ለመላ የኢትዮጱያ ህዝቦች ካለፉት ገዥዏች የተለዬ ምን ለውጥ አመጣልን ???




የየካቲት 11  42ኛ  የህወሐት በአል ሲከበርና ፈይዳው ፣
——————————————————
ለካቲት 11 / 6  /67 /ዓ ም  ወደ ደደቢት በረሐ ስንዘምት የነበረን  አላማ  የደርግን ስርአት አስወገደን   የተሻሻለች ሁሉም አይነት  ሰብአዊና ዲሞክራሲ መብቶች የሚከበሩባት ፣  የህግ የበላይነት የሚረጋገጥባት፣ የተለያዬ ፖለቲካ  አስተሳሰብ  ያላቸው ፖለቲካ ሀይሎች በሰላምና በነጻነት  የሚንቀሳቀሱባት፣ የበለጸገች ኢትዮጱያ  ለመመስረት  እንዲሁም ፣ የላሸቀው  በስብሶ የነበረ ስርአት በማስወገድ  ፍትሐዊ  የሆነ  ከሙሱናና  የተበላሸ  ስርአት የጸዳ ስርአት ለማምጣት ነበር ።
በተጨማሪ  በሀገራችን  ዜጎች በእኩልነት እንዲኖሩ ፣ የተመጣጠነ  የኢኮኖሚ ክፍፍል እንዲኖር ፣ የዘር  የእምነት  የቢሄር ልዩነትና መናናቅ እንዲወገድ ፣ ድኽነት ስደት እንዲጠፍ እንዲወገድ ፣ ለማድረግ ነበር ።
የሁሉም  ኢትየጱያዊ  ማህበራዊና እኮኖሚያዊ  ችግሮች  እንዲቀረፉ  ማድረግ ፣ በተለይ ደግሞ የገጠር ኃላቀር  ንሮና   መሬቱ በመሳፍንቶች  እጅ ስለነበር አርሶአደሩና  የከተማ ነዋሪ የመሬት ባለቤትነት እንዲነረው ታሳቢ በማድረግ ነበር  ወደ ደፈጣ ውግያ  የዘመተው ።
በሀገራችን  የቢሄር ቢሄረሰብ  መብቶች እንደከበሩ  በማኸላቸው የነበረ ግጭት ቂም  በቀል   በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ  የነበረው  የባላባታዊ  የመሳፍንቶች  ዘውዳዊ  ሰርአትና   ለዘውዳዊ  ስርአት  ገልብጦ በሀይሉ ስልጣን  የያዘ  ወታደራዊ ስርአት  በማስወገድ  በመቃብራቸው  በህዝብ  የተመረጠ ህዝባዊ መንግስት  እንዲመሰረት  ለመታገል ነበር  ።
ሌላ ከአድልዏ የጸዳ የትምህርቲ ፣ የጤና  ፓለሲ እንዲኖር ፍትሀዊ በሆነ የትምህርት የመታከም  መብት  እንዲኖር   ፣ የዘውዳዊና የደርግ ባለስልጣናትና የቤተሰቦቻቸው  ቅምጥል ቀርቶ የዜጎችን  እኩል ተገልጋይነት እንዲኖር ነበር ።
በሀገራችን  በመንግስትና  በፓርቲ በለስልጣናት በባለቤትነት የሚያዝ ወይ የሚታወቅ   የንግድና  የእንድስትሪ ተቋማት እንዳይ ነሩ ፡ በሀገራችን የግለሰው  እና የሀብት ባለቤትነት
           ክፍል አንድ የነበሩ አላማዎች ፣
          ————————————
የየካቲት 11  42ኛ  የህወሐት በአል ሲከበርና ፈይዳው ፣
——————————————————
፠፠     ሀወሐት በ42 አመት በትግልና በስልጣን  አገዛዙ  ዘመን   ለትግራይ ህዝብ ብለው ለመላ የኢትዮጱያ  ህዝቦች
ካለፉት ገዥዏች  የተለዬ ምን ለውጥ አመጣልን ???
፠፠  ለካቲት 11 / 6  /67 /ዓ ም  ወደ ደደቢት በረሐ ስንዘምት የነበረን  አላማ  የደርግን ስርአት አስወገደን   የተሻሻለች ሁሉም አይነት  ሰብአዊና ዲሞክራሲ መብቶች የሚከበሩባት ፣  የህግ የበላይነት የሚረጋገጥባት፣ የተለያዬ ፖለቲካ  አስተሳሰብ  ያላቸው ፖለቲካ ሀይሎች በሰላምና በነጻነት  የሚንቀሳቀሱባት፣ የበለጸገች ኢትዮጱያ  ለመመስረት  እንዲሁም ፣ የላሸቀው  በስብሶ የነበረ ስርአት በማስወገድ  ፍትሐዊ  የሆነ  ከሙሱናና  የተበላሸ  ስርአት የጸዳ ስርአት ለማምጣት ነበር ።
፠፠  በተጨማሪ  በሀገራችን  ዜጎች በእኩልነት እንዲኖሩ ፣ የተመጣጠነ  የኢኮኖሚ ክፍፍል እንዲኖር ፣ የዘር  የእምነት  የቢሄር ልዩነትና መናናቅ እንዲወገድ ፣ ድኽነት ስደት እንዲጠፍ እንዲወገድ ፣ ለማድረግ ነበር ።
፠፠    የሁሉም  ኢትየጱያዊ  ማህበራዊና እኮኖሚያዊ  ችግሮች  እንዲቀረፉ  ማድረግ ፣ በተለይ ደግሞ የገጠር ኃላቀር  ንሮና   መሬቱ በመሳፍንቶች  እጅ ስለነበር አርሶአደሩና  የከተማ ነዋሪ የመሬት ባለቤትነት እንዲነረው ታሳቢ በማድረግ ነበር  ወደ ደፈጣ ውግያ  የዘመተው ።
፠፠    በሀገራችን  የቢሄር ቢሄረሰብ  መብቶች እንደከበሩ  በማኸላቸው የነበረ ግጭት ቂም  በቀል   በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ  የነበረው  የባላባታዊ  የመሳፍንቶች  ዘውዳዊ  ሰርአትና   ለዘውዳዊ  ስርአት  ገልብጦ በሀይሉ ስልጣን  የያዘ  ወታደራዊ ስርአት  በማስወገድ  በመቃብራቸው  በህዝብ  የተመረጠ ህዝባዊ መንግስት  እንዲመሰረት  ለመታገል ነበር  ።
፠፠  ሌላ ከአድልዏ የጸዳ የትምህርቲ ፣ የጤና  ፓለሲ እንዲኖር ፍትሀዊ በሆነ የትምህርት የመታከም  መብት  እንዲኖር   ፣ የዘውዳዊና የደርግ ባለስልጣናትና የቤተሰቦቻቸው  ቅምጥል ቀርቶ የዜጎችን  እኩል ተገልጋይነት እንዲኖር ነበር ።
፠፠  በሀገራችን  በመንግስትና  በፓርቲ በለስልጣናት በባለቤትነት የሚያዝ ወይ የሚታወቅ   የንግድና  የእንድስትሪ ተቋማት እንዳይ ነሩ ፡ በሀገራችን የግለሰው  የዲሞክራሲ  መብቶች  እና  የሀብት  የግል ባለቤትነት ገዥና የበላይነት  እንዲ ነረው ነበር  የታገልነው እና  በሞቶ ሽዏች  የሚቆጠሩ ወጣቶች ሂወት የከፈሉበት  ። በዛው ልክ አካላቸው የጎሉበት  ትግል  አሁን በመሬት የምናየው ያለን  ጉድ አልነበረም ።
፠፠  የዘውዳዊ ስርአት የሲ አይ  ኤ የስለላ መረብና የመንግስቱ ሃይለማርያም   የከጅቢ ስለላ ወጥመድ  ህዝባችን  እንዲላቀቅ አላማ ነበረን ።
፠፠  የህወሐት የ42  የልደት በአል   የተመሰረተበት   በአል ሲከበርስ  በምን ደረጃ እንገኛለን  ????  እንግዲህ  የ42 አመት ጉዞው ስመለከተው  ኢትዮጱያ ሀገራችን በተለይ ደግሞ  ያቺ  በአድልዏ  ለምታና  በልጽጋ   የምትባለው 5ሚሊዮን  የተጨቆነ ህዝቢ ያላት የትግራይ ክልል   በሚከተሉት ነጥቦች ይገለጻል ።
———————————————————
፠፠   የዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ  መብቶች  የህግ የበላይነት  ለሽታውም የማይታይበት  የአፈና ሞደል የሆነች  አገርና ህዝቦቻ እየተመለከትን  ነው።
፠፠    የዜጎች በነጻ የመደራጀት መብት የተከለከለች  የተወዳዳሪ ፖለቲካ   ፓርቲዏች በነጻ እንዳይንቀሳቀሱ  የተዘጉባት ፣ እንዳውም የፓርት መሪዏች ፡አባሎቻቸው ፣ ደጋፊዏቻቸው  በሀገሪቱ እሱር ቤቶች  የታጎሩባት   ፡ በአጠቃላይ  የቡዛንነትን  ነጻ ተሳትፎ የከሰመባት አገር እየተመለከትን  ነው ።
፠፠      በተለይ በአሁኑ ጊዜ  ዲሞክራሲያውያን የሆኑ የፓርቲ መሪዏች ፣ ጋዜጦኞች ፣ የፓርት ደጋፊዏች  በማሰር በመሰቃየት በአለም  የታወቀች  አገር የሆነች አገር እያየን ነው ።
፠፠ የህትመት ውጤቶች  ነጻ ፕሬስ ፡ የማህበራዊ  ሚድያ  ፣ የመናገር  የመጻፍ ፣ በፈለከው ሚዲያ ለመናገር የተከለከለበት ። የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ፣ የመሰብሰብ ፣  በመንግስት ሚዲያም አንባ ገነኑ ስርአት ከሚፈልገው  ውጭ ለመናገር የማትችልበት  ሁኔታ ያለንበት  4
የህወሐት 42ኛ የልደት በአል  ሲከበር እያየን ነው ።
፠፠   የደርግን  ፋሽሽታዊ  ወታደራዊ አስተዳደርና  አዋጅ ከ 42    አመት በኃላ  ያገረሸባት አገር  ፣ ዜጎች በጅምላ እየተገደሉ እየታሰሩባት ፣ ካገር ውጭ እየተሰደዱ ጭራሹም የዲሞክራሲ ሽታ የማናይባት አገር እያየን ነው።
፠፠  የሀገራችን መሬት ገንዘብ ኩባንያዏች  እንሽራንሾች ፣ባንኮች ፣ እንድስትሪዏች ፣ በመላው ሀገሪቱ ያሉ ህንጻዏች ፡ የትራንስፖርትና  ኮንስትራክሽን ኩባንያዏች፣  የኮንስትራክሽን  ማሽነሪዎች በገዥ ፖርቲ ባለስልጣናት፣ ዘመድ አዝማድ በሞኖፖ ተወረው የተያዙባት የካቲት 11  42ኛ የሀወሐት የልደት በአል ።
፠፠ ለአምስት  ጊዜ የተደረገው  የሀገር  ፓርላማ    ምርጫ የተወዳዳሪ ተቃዋሚ ፓለቲካ ፓርቲዏች የድምጽ ካርድ ሙሉ በሙሉ የተሰረቀበት  ።  በተለይ ደግሞ  በ4ኛ እና  5ኛ  የምርጫ   ዘመን  ህወሐት ኢህአደግ  96.6% እና 100%  አሸንፈናል ያሉበት አስነዋሪ ተግባር የሰሩበት  ፣ ኃላም  ተቃዋሚ ፓርቲዏች እንዳያንሰራሩ  አፍነው በማያዝ  እንቅስቃሲያቸው  በአንድ  ለአምስት የነበረ  የስለላ ወጥመድ አሁን ደግሞ የስለላ ወጥመዱ  ወደ አንድ ለአንድ  የስለላ መዋቅር  በማፈን የሆነ እንቅስቃሴ   እንዳይደረግ
በማፈን  የምትከበር ያለች ለካቲት 11  ናት ። በተጨማሪ ከምርጫ በኃላ ቢሆንም ቡዙ የፓርቲ  መሪዏችና አባሎቻቸው እጩ ተወዳዳሪዎች የታሰሩበት አሁንም እየታሰሩ  ወይ በክስ የቁም እስሮኞች ሆነው  የሚኖሩባት 42ኛ የካቲት 11  ናት ።
፠፠ በዝች አገር ቡዙ ቡቁ  ሙሁራኖች  የተገለሉበት  ብቁ ያልሆኑ ለስሙ ደገተር ፕሮፌሰር  የሚል ስም ተለጥፎባቸው  አገሪቱ ለብልሽት  የተዳረጉባት  በአል እያከበርን ነው ።
፠፠ በሀገራችን ማንም ፓርት  ህወሐት  ኢህአደግ ጭምር በቀጥታ  ይሁን  በተዘዋሪ  በንግድና በእንድስትሪ መስራት አይችልም በሚል ህገመንግስትታዊ ድንጋጌ  በመጣስ እንደ የህወሐት እና  የበአዴን አማራር ቢሊየነር የሆነባት የካቲት በአል እንድናከብር እንገደዳለን ።
፠፠  ህወሐት   በአሁኑ ጊዜ  ታደስኩ እያለ  የውሸት ተሀድሶ  በመታጠቅ እያታለለ  ይገኛል ።  የዘንድሮ የውሼት ተሀድሶ  ግን ህዝቡ ስለነቃባቸው  የህዝብ የአስተሳሰብ አቅጣጫ ለመቀልበስ ነው እንጅ  ህወሐት በአሁኑ ጊዜ  ሊታደስ አይችልም  ።
፠፠  የዘንድሮ የህወሐት 42 አመት የልደት በአል ስናከበር  የሀገራችን ልኡላውነት እንደተደፈረ እና  እንደ ተወረድን የሚከበር ያለው በአል ነው ።
፠፠   በዚሁ 42ኛ የለካቲት  በአል ስናከብር  የተጀመሩ  ፕሮጆክቶች  በሙሱና ምክንያት ያልተጨረሱ  የተጨረሱም ጥራት  የገደላቸው  ከመሆኑም በላይ  አገልግሎት  ሳይሰጡ እየፈረሱ መሆናቸው  በተለይ ደግሞ በትግራይ ክልል  የስፓልት መንገዶች  የውሀ ግድቦች ፣ የውሀ ጉድጓድ   አገልግሎት  ሳይሰጡ ፈርሰዋል ። ወይ ደርቀዋል  ፣ ለምሳሌ  በትግራይ  ክልል ከተቆፎሩት  የውሀ ጉድጓድ  ከ90%  በላይ ደርቀዋል ። ምክንያቱም ከጅምሩ ሲቆፈር ጥናት ያልነበረው ስለሆነ  ነው ።   የኮንደምኔም ህንጻዏች ተሰርተው ሳይጨረሱ የፈረስበት ሁኔታ አለ ። በአድዋ 14 ህንጻዏች  ቁመናቸው ካለቀ በኃላ የፈረሱ  አሉ  መኖርያ   ሊሆኑ አይቹሉም ። በመቀለ ፣በአዲግራት በሌሎች ከተሞችም ጭምር ። ተሰርተው ሰው የሰፈራቸውም ባጭር ጊዜ ወዳቂዎች  ናቸው ።
፠፠ የትግራይ  ህዝብ  በ25 አመት  የህወሐት  አገዛዝ ከሰፍትኔት እና ከሌሎች እርዳታ ሰጭዎች  ጥገኝነት አልዳነም  የሰፍትኔት  አሰጣጥም  ቀዳምነት  ለታማኝ  የህወሐት አባላት ነው የሚሰጥ ፣ አባል ያልሆኑ   ታማኝ ያልሆነ  የሰፍትኔት ፣  ለአደጋ ተብሎ የሚሰጥ ሰንዴና የቅባት  ምግቦች አድላዊ አከፋፈል ነው የሚደረግ  ። ሌላ ከዚህ  ጋር ተያይዞ መታየት  ያለባቸው በአሁኑ ጊዜ እድሚያቸው ከ15   እስከ 45 ከዛ በላይ ያሉ ዜጎች  በሙሉ ለማለት ይቻላል   ወደ ስደት ተበታትነዋል  ።  እንግዲህ  42 አመት የህወሐት በአል ከለይ የተዘረዘሩት ችግሮች  ነው  ይዞልን  የመጣ።
፠፠   ህወሀት ባለፉት  42 አመታት የሀገራችን  ሉአላውነት እንዲጠበቅ ወይ እንዲከበር አላደረገም  ። እንዳውም በህዝብ፡በሰላም የሚታገሉ  ፓርቲዏች  ስለየሀገር ሉአላውነት ይከበር  ብለው ጥያቄ ሲያነሱ በጠላትነት  ይፈረጃሉ ። ህወሐት ህዝባችን ከነ እንስሳ ዘቤታቸው ታፍሰው  በኤርትራ በረሀ የባርያ አገዛዝ እየተፈጸመ  ፡ በሱዳን ፡ በሱዑዲ ህዝባችን ግፍ ሲደርሰው  የሚጣበቅለት አካል አልታየም ። በመሆኑ የዘንድሮ 42ኛ የህወሐት የልደት በአል ሲከበር ሉአሏዊነት ሀገርና ህዝባችን በተዋረደበት  ጊዜ የሚከበር  ያለ በአል  ነው ።
፠፠ ህዝባችን የ31 ኩባንያ ቢሌኖሩ  ትእምት  በሀዝብ ስም በመነገድ  የህወሐት መሪዏች ከነልጆቻቸውና ከነ ዘመድ አዝማዳቸው  ተንደላቅቀው የሚኖሩባትትግራይ ፣ በተመሳሳይ በሞቶ ሽዎች የትግራይ  አካልጉዳቶኞች ስም በነ አስመላሽ ወልደስላሴ  የመንግስት ተጠሪ ምኔስቴር ፡ በአጽብሀ አረጋዊ  የእንባስነይት  ህዝብ  አንተ አትወክለንን  ብሎ የገለለው ፣  ሁለቱ የፓረላማ አባላት  የሚመሩት ቢሌኖሩ የአካል ጉዳተኞች ማህበር  ተንደላቅቀው የሚኖሩባ ትግራ  በአንጻሩ   ህቦቻ ለሰደት ለስራ  አጥነት የተዳጉባት  ያቀፈች  ትግራይ  እያየንባት  ለካቲት 11።
፠፠ 26 አመት ሙሉ  ንጹህ  የሚጠጣ ውሀ የተነፈገባት  ትግራይ፡ የመቀሌ ከተማእንካን ጭራሹ የው ሽታ የለላት የዝነድሮዋ  42 ኛ የካቲት  ሆና አለች ።
፠፠ በዘንድሮዋ ለካቲት  42 ኛ በአል  አይኑ ያፈጠጠ ሙሱና የበላይነት  የያዘበት ፣ የውሸት ተሀድሳቸው   ሙስና እና ኪራይ ሰብሳቢነት  እናስወግዳለን ቢሉንም ሁሉም ሆዳሞች በመሆናቸው  ተሻሽተው ተሻሽመው  ለ100 ሚሊዮን የሸወዱባት ለካቲት 11
፠፠  የህወሐት መሪዏች  የትእምት ኩባንያዎች የህዝብ  ናቸው ብለው ለመሸወድና ለምዝበራቸው  ሸፋን ይሆንላቸው  ዘንድ  ትምሀርት ቤት ሰራን ፣ አሁን ደግሞ ለካቲት  11  ሽፋን በማድረግ  የተሰው ቤተሰብ ሽልማት ለመስጠት ሽርጉድ እያሉ ይገኛሉ ።  የትግራይ ህዝብ ግን ምጽዋት አይደለም የሚፈልገው ፣ እያለ ያለው  ከ31 በላይ  ኩባንያዏች በየአመቱ በአስር ቢሊዮን የሚቆጠር ብር  እየዛቃችሁ ያላችሁ አስረክቡን በራሳችን ቦርድ ዳሪክቶሮች  እንምራቸው  አለን  እያለ ነው ። የዘንድሮዋ የ42ኛ የካቲት በአል ግን  የሚዋጥላችሁ አልልሆነም ።
፠፠    42ኛ ለካቲት 11  በሀገራችን ያሉ የመንግስት ሰራተኞች ስቢክ ማህበራት አንድ ለአንድ የሰለላ ወጥመድ ሰንሰለት በመዘርጋት  ዜጎች እርስ በእርሳቸው  እንዲጠራጠሩ እና እንዲጣረሱ በማድረግ አንድነታችን እንዲላላ አድርገዋል ይህደግሞ የዘንድሮ ለካቲት ለጆችያመጣችሁን ጣጣ  ነወ።
፠፠     በዝህቺ ለካቲት 11  የትግራይ ህዝብ ከሌላ ኢትየጱያዊ ወንድሙ በክፉ አይን እንዲተያይ ፣ እዲጠራጠር ተደርገዋል  ። የማይናቅ ቁጥር ያለው ኢትዮጱያዊም  ለከፋፍለህ አገዛዛቸው  እንዲመች  ለሚሰሩት ተንኮል  ሌጋሲ በመከተል  በድሀ ወንድሙ ኢትዮጱያዊ ትግራዋይ ጥላቻ እያሳዮ ይገኛል ። ይህ ድርጊት ደግሞ  ለከፋፋዮች  አላማ ያሳካል ።
፠፠   የለካቲት 11  42ኛ የህወሐት በአል በውሼት ተሀድሶ ታጅቦ  በሀይለማርያም  ደሳለኝና አጋፋሪዎቹ  በትግራይ ህዝብ የውሼት ልማት በተቀናበረ የውሼት ቃላት ለዎሶ ሊያሰማን ተዘጋጅቶ ይገኛል ።
፠፠ በዚሁ በአል በመላው ትግራይ ያለው የተቃጠለ ቆሽጥ ተጽፎ በተሰጣቸው  እንደ ገደል ማሚቶ ይጭሁብን ይሆናል ።  የትግራይ ህዝብ ግን  ለሚደረገው  የውሼት ዲስኩር  ከመጤፍም አይመለከተውም ።
፠፠   በነገይቱ ለካቲት 11 ከጠ/ም /ሀይለማርያም ደሳለኝ ለ20 አመት  ያህል ዜጎች የዜግነት  የማይሸራረፍ  መብት እያለ  መጠለያ ቤት ሰርተው እንዳይኖሩ  ተነፍጋቸው  መሬታ እና አንጥራ ሀብታ ለኢህአደግ ባለስልጣናትና ዘር ዘራቸው  ተችራ ቆይታ  እነዚህ ሰወች ከሁለት በላይ ህንጻዏች ሰርተው በውጭ ምንዛሪ እያካረዩ  ፣ ለራሳቸው ግን በመንግስት ምርጥ ቤት እኖሩ ተንደላቅቀው  እየኖሩ  በአንጻሩ የትግራይ ህዝብ በውድ ኪራይ እየኖረ  ስለመረረው ፣
፠፠  ዘንድሮ ግን ህዝብ መሮት ለአመጽ  ሊነሳ ጥያቄ በማብዛቱ ሰግተው 70 ሜትር ከሪ  መሬት ቤት መስርያ  ለማስታገሻ መሬት ሰጥተውት  ስላሉ በመቀሌ ያካፋፈሉት የ11  000  መኖሪያ ነገ መሰረተ ዲንጋይ  ያስቀምጣሉ ። በተጨማሪ ያው ጤቱ ሀዘን ነው ልቅሶ ገና ያልታወቀ  የእንድስትሪ ዞን ይገበኙ ይሆናሉ ። በተጨማሪ  በተቀመጠለት የግዜ ገደብ ያላለቀ የአባይ ጸሀዬ የዛሬማ ሽኮር ፋብሪካ ይጎበኛሉ  በተረፈ የትጃሩ የህወሀት መሪዎች  ኩባንያዏች  ይገበኛሉ  ይባላል ::
ከአስገደ ገብረስላሴ ፣
8/6 /2009 ዓ ም ፣
ይቀጥላል !!

No comments:

Post a Comment