Sunday, February 19, 2017

ኑ፣ የካቲት 12 ሰማዕታትን መታሰቢያ ዕለት በፌስቡክ እንክብር።

ኑ፣ የካቲት 12 ሰማዕታትን መታሰቢያ ዕለት በፌስቡክ እንክብር።

 
By ሳተናውFebruary 19, 2017 00:07


 3  83  87
አገር ከወረረው አገሩን ለወራሪው የሸጠው ይብሳል!
የካቲት አስራ ሁለት የሰማዕታት ዕለትን የተለያዩ ታሪኮችን እያስታወስን እናስበው። ሙሉ በሙሉ ኢትዮጲያዊ ነኝ ብለን መናገር የምንችለው ታሪካችንን በሚገባ ስናውቀው ነው። ፓስፖርት ብንቀይር አክስንታችንን ብንለውጥ ኢትዮጲያውነታችንን ግን መደብቅ አንችልም።
ጥሊያን በሄደበት እና በወረራቸው አገሮች የሚቀጥራቸው ቅጠረኛ ሹም ባሻህወችን የሚያለብሳቸው በስተቀኝ በኩል የሚታየው አይነት ነጭ ወይም ካኪ መለዮ ነው።
በስተግራ ያለው ደግሞ በራስ አበበ አረጋይ እና በደጃዝማች ሙሉጌታ ብሊ የተመራው በውሮጳ አቆጣጠር 1936 ማይጨው ላይ እጅግ ዘመናዊ በሆነ የጦር መሳሪያ እና በአየር በታጀበው የፍሽስት ወታደር የተሸነፈው በታሪክ የመጀመሪያው የኢትዮጲያ ጦር ሠራዊት መለዮ (uniform) ነው። ከዚህ በፊት የኢትዮጲያ ሠራዊት መለዮ ወይም Uniform አልነበረውም።
ከዚህ ሽንፈት በኋላም የኢትዮጲያ ጦር መለዮ ለባሽ አልነበረም,። ሁሉም ከየታዛው መንደሩ እና ቀበሌው እጀ ጠባቡን እና ኩታውን ለብሶ ነው በባዶ እግሩ ሚስቱን ልጁን ትቶ በፋሽስት ጦር ላይ የዘመተው። በውሮጳ አቆጣጠር በ1941 ንጉሰ ነገስቱ ከእንግሊዝ አገር ሲመለሱ እንደገና በድጋሚ ዘመን ቀመስ መለዮ የለበሰ፣ የብረት ቆብ የደፋ ቀበቶ የታጠቀ ብረት የነገተ ፣ የጦር ሠራዊት አቋቋሙ።

No comments:

Post a Comment