Friday, February 10, 2017

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከተወሰኑ የአፍሪካ ሐገራት ማግኘት የነበረበትን 220 ሚሊየን ዶላር ማግኘት እንዳልቻለ ተሰማ… – (ንጋቱ ሙሉ)



አየር መንገዱ ከናይጄሪያና ግብፅ እንዲሁም ከሌሎች የአፍሪካ ሐገሮች ነው 220 ሚሊየን ዶላሩን ማግኘት ያልቻለው ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናይጄሪያና ግብፅ እንዲሁም ሌሎች የአፍሪካ ሐገራት አገልግሎት የሰጠበትን ክፍያ ማግኘት ቢኖርበትም ሐገራቱ በነዳጅ ዘይት ዋጋ ማሽቆልቆል የተነሳ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ስላጋጠማቸው የአገልግሎቱን ክፍያ በዶላር መቀበል እንዳልቻለ ነው የተወራው፡፡
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ጉዳዩ ፈተና ሆኖብናል ሲሉ ነግረውኛል ብሎ መረጃው ፅፏል፡፡
ዩናይትድ ኤይርላይንስ እና ኤምሬትስ የመሳሰሉት አየር መንገዶች ናይጄሪያ የገጠማትን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት አድርገው ወደዚያች ሐገር አንበርም ባሉበት ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በበኩሉ ናይጄሪያን በክፉ ጊዜዋ ከጎኗ አልርቅም፣ በረራዬም አይቋረጥም ማለቱ ይታወሳል፡፡
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ስለወሬው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም፡፡

No comments:

Post a Comment