Saturday, February 11, 2017

የብአዴን ፅሕፈትቤት ለኢህአዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ ፃፈው የተባለው ሪፖርት

የብአዴን ፅሕፈትቤት ለኢህአዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ ፃፈው የተባለው ሪፖርት እነሆ (ብአዴን ኢህአዴግ መሆኑ አንርሳ። ኢህአዴግም የህወሓት የእጅ ስራ ነው። በህወሐታዊ ድርጅት ኢህአዴግ ውስጥ ምን እየተደረገ እንደሆነ ለማወቅ ሪፖርቱን እናንብብ። ህወሐት የሚያመጣው ጣጣ! ሳንበላ በሉ! ደግሞኮ በህወሐት-ኢህአዴግ በራሱ መፃፉ ነው የሚገርመው)
————
የብአዴን ጽ/ቤት ለኢህአዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት የመምህራን መድረክ ማጠቃለያ ሪፖርት ከላከው የተቀነጨበ – Reference Number: ቁጥር ብአዴን /ማዕ.ኮ/2131ሪ ቀን 23/05/2009 ዓ.ም.
ምሁራኑ ስለ ህወኃት እና ትግራይ የሚከተለውን ዘመን ተሻጋሪ እውነታ አስቀምጠዋል፡፡
1. ፍትሀዊ የሆነ የሀብት ክፍፍል የለም፡፡ ሁሉም ነገር ወደ ትግራይ ነው፡፡
2. ጥሬ ሀብት ከአማራ እየተመረተ ፋብሪካው የሚገነባው ትግራይ ነው፡፡
3. ትግራይ እስካሁን ሲወስድ የነበረው ኢንዱስትሪዎች፣ በጀት ና ትልልቅ የስልጣን ቦታዎች ነበረ አሁን አሁን ግን ቅርሶችን ልክ እንደ ላልይበላ፣ ዳሸን ተራራን የትግሬ ነው በማለት ታዋቂነታቸውን በመጨመር ለልማት አጋዥ አቅም እየጨመሩ ነው፡፡
4. ትግራይ መሬት የማስፋፋት ስራ እየሰሩ ነው፡፡
5. አሁን በተደረገው የመምህራን ስብሰባ ትግራይ አበል ሲከፈል እኛ ጋር አይከፈልም ይህም ትግራይ የበላይነትና ጥንካሬን የሚገልጽ ነው፡፡
6. የወልዲያ የሀራ ገበያ መቀሌ የሚገነባው የባቡር መስመር አማራን ለመጥቀም ሳይሆን ለትግራይ ታስቦ የሚሰራ ነው ለእኛ ያለው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የለውም፡፡ እዳውም አማራ ላይ እዳይፈተሸ እና ከምሀል ሀገር እና ከወደብ በቀጥታ ትግራይ እንዲገባ በማስብ ከከተማ በርቀት የአማራን ክልል ገጠር ወረዳዎች እየነካ ነው የሚያልፈው፡፡
7. የሰሜን ወሎዋ ‹‹ዋጃ›› ወደ ትግራይ የተከለለው በህዝቡ ፈቃድ ሳይሆን በግዳጅ ነው፡፡
8. የውጭ ጎብኝዎች ሲመጡ ቅድሚያ የማስተዋወቅና እንዲሄዱ የሚደረጉት ወደ ትግራይ ነው፡፡
9. ላስታ አቡነ የወሴፍ ላይ እየተሰራ ያለው የህዋ ምርምር መቀሌ ዩኒቨርስቲ እንዲመራው መደረጉ በሂደት ወደ ትግራይ ለማካለል የሚደረግ ሴራ ነው፡፡
10. ወልቃይት ጥንት ጀምሮ የአማራ የጎንደር መሬት ነው መመለስ አለበት፡፡ ከዋጃ እስከ ኮረም ያለው ወደ ትግራይ መከለል አልነበረበትም አሁንም መመለስ አለበት፡፡
11. የአሸንደዬ በአል በአማራም በትግራይ እንደሚከበር ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በዩኒስኮ የተመዘገው ግን የትግራይ ነው፡፡
12. አጼ ዬሀንስ ሙስሊሙን ሲገድልና ሲያጠምቅ ለነበረው የተቀመጠ ነገር የለም ነገር ግን ሚኒሊክ ጡት ሳይቆርጥ እንደቆረጠ ተደርጎ አኖሌ ሀውልት መታሰቢያ ተሰራ፡፡
13. ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህወሀት አመራር ታዛዥ ነው፡፡
14. አንቀጽ 39 መሰረዝ አለበት ትግራይም ግዛቱን ለማስፋፋት የሚሯሯጠው በሂደት ለመገንጠል ነው፡፡
15. የፌደራሊዝም ስርዓት ለኢትዮጵያ አይበጃትም፤ በፌደራል ሽፋን የአንድ ብሄር የበላይነት እየተገነባ ነው፡፡
16. ኢትዮጵያ ውስጥ የዜግነት ደረጃ አለ፤ ቀዳሚው ትግሬ ነው፡፡
17. የብአዴን አመራር ለአማራ ህዝብ እድገት እየሰራ አይደለም፡፡ ያሉት ልማቶች ከትግራይ ክልል ጋር ሲነጻጸር በፋብሪካም ሆነ በሌሎች ልማቶች በእጅጉ ያነሰ ነው፡፡
18. ብአዴን የሚመራው በህወሀት ነው እራሱን ችሎ አይመራም፡፡
19. በከፍተኛ ደረጃ የአማራ አመራር የለም፡፡ ያሉትም አመራር በአማራ ሽፋን የሌሎች ብሄር ዘር ያላቸው ናቸው፡፡ ለአብነት አዲሱ ሀረር፣ በረከት ኤርትራዊ፣ ካሳ ተ/ብርሀን ኮረም ፣ ህላዊ የወሴፍ ደቡብ ናቸው እነዚህ በአማራ ስም ያሉ ናቸው፡፡ እንዴት ለአማራ ሊቆረቆሩ ይችላሉ፡፡
20. የአማራ ህዝብ በሌሎች ብሄሮች ጥላቻ እንዲፈጠርበት ሆን ተብሎ እየተሰራበት ነው፡፡ ለአብነት የአኖሌ ሀውልት፣ ትምክህተኛ እያሉ መፈረጅ
21. ትምክህትና ጠባብ አመለካከቶች መሰጠት ያለበት ለትግራይ ነው፡፡
22. በ10ኛ ክፍል የስነ ዜጋና ስነ ምግባር መጽሃፍ በትግራይ እና በአማራ ክልል መካከል ያለው የድንበር ስህተትም ሆነ በ6ኛ ክፍል የእንግሊዘኛ መጽሀፍ ራስ ዳሸን በትግራይ ክልል እንዳለ ተደርጎ የተቀመጠው ሳይታሰብ ሳይሆን ሆን ተብሎ የተፈጠረ ሴራ ነው፡፡ ምክኒያቱም ትምህርት ሚኒስተር ችግሩን ካወቀበት ቀን ጀምሮ እንኳን ለረዥም ጊዜ ሳይታረም የታለፈ መሆኑ፤ ሌላው ይቅርታውም የህዝብ ጭጭት ግፊት እንጂ ከልብ የመነጨ አይደለም በህግ መጠየቅ ይገባል፡፡
23. አዲስ ከተሾሙት ሙሁር መሳዩች ጀርባ የትግራይ በላስልጣናት እጆች እንዳሉ እናውቃለን፡፡ ለአብነት ከዶር ነገሬ ሌንጮ ጀርባ ዛዲግ አብርሃ የሚባል የሚዲያ ጠላት አለ፡፡ እና እንዴት ሁኖ ነው ፕሬሱ ነፃ የሚሆነው፡፡
24. በአገራችን የአንድ ብሄር የበላይነት አለ፡፡ ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል እና የአስተዳደር ሁኔታ የለም፡፡
25. የአማራና በትግራይ መካከል ያለውን የድንበር ችግር ፌደራል መፍታት ነበረበት ለክልሎች መግፋቱ ስህተት ነው፡፡

No comments:

Post a Comment