Sunday, February 19, 2017

ወያኔ ወደ ደቡብ ሱዳን ሰራዊት እያስጠጋች ነው!



አሶሳ ጊዘን ለደቡብ ሱዳን ቅርብ የሆነች በጣም ሞቃታማ የወረዳ ከተማ ነች። በዚሁ በኩል ብዛት ያለው የወያኔ ሰራዊት ማታ ከ4:00 ሰዓት በኃላ የማቅረብ ስራ በ09/02 009 ዓ.ም ሰርቷል። በርግጥ ወደ ውስጥ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ይግቡ ድንበሩ ላይ ይመሽጉ እያጣራን ነው። የስደተኞች ካምፕ እዚያው አካባቢ ይገኛል፡፡ የአካባቢው ሰው በማያይበት እና ባልሠማበት ሁኔታ ነው ይህን እየፈፀሙ ያሉት። ወያኔ ከደቡብ ሱዳን ጋር ያላት ችግር እየተወሳሰበ መሄዱ ሲዘገብ ቆይቷል። ግብፅም እዛ የሚሊታሪ ቤዝ ማቋቋሟ ይታወቃል። እዛ አካባቢ መንጌ ወረዳ ሸርቆሌ እና ጊዘን ወረዳዎች አካባቢ ያሉ የበርታ ማህበረሰብ ተወላጆች በትግራይ የእርሻ ኢንቨስተሮች እና ወርቅ አውጪዎች ስለተበደሉ የሚሸፋቱና የሚወጉት ተፈጥረዋል። የአባይ ግድብ ጀርባም ነው። ግብፅም ከሞከረች እጇ የሚረዝምበት መሿለኪያ ቦታ አለው፡፡
ሙሉነህ ዮሃንስ

No comments:

Post a Comment