Thursday, April 28, 2016

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ተባረሩ

3

8b0067e1ba18cd789b122c804be56585_XL
(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ አቶ ዮሐንስ ሳህሌ ከአሰልጣነታቸው መባረራቸው ተሰማ:: በአንድ ወር የ75 ሺህ ብር ተከፋይ የነበሩት እኚሁ አሰልጣኝ ብሄራዊ ቡድኑን ከሚያዝያ 26/2007 ዓ.ም ጀምሮ ሲያሰለጥኑት ቆይተዋል::
የቀደሞው የደደቢት እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ አቶ ዮሐንስ ሳህሌ ከአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው የተረከቡትን ብሄራዊ ቡድን ውጤታማ ሊያደርጉ ይችላሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ቢሆንም በ እርሳቸው ዘመን ብሄራዊ ቡድኑ የሶማሊያ ብሔራዊ ቡድንን ከማሸነፉ ውጭ ምንም አመርቂ ውጤት አላመጡም እየተባሉ በስፖርት ተንታኞች ዘንድ ሲተቹ ቆይተዋል::
75 000 ብር ወርሃዊ ደመወው; ተሽከርካሪ ከሾፌር ጋር እንዲሁም ባለመስመር የሞባይል ስልክና የጤና ኢንሹራንስ ከተለያዩ ጥቅማትቅሞች ጋር እየተከፈላቸው ብሐራዊ ቡድኑን ሲያሰለጥኑ የነበሩት አቶ ዮሐንስ በተጨማሪ ምክትል አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ እና የበረኞች አሰልጣኝ አሊ ረዲም አብረው መሰናበታቸው ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለከታል::

No comments:

Post a Comment