Saturday, April 16, 2016

ጋምቤላ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ ሰዎች ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገደሉ።


ጋምቤላ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ ሰዎች ዐርብ ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገደሉ።
የኑዌር ጎሳ አባላት የመኖሪያ መንደሮች ላይ ባነጣጠረው ጥቃት የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከ221 በላይ መሆኑን ሱዳን ትሪቡዩን ዘግቧል።
ሱዳን ትሪቢዩን የደቡብ ሱዳን ጦር መለዮ የለበሱ እና የታጠቁ በሺዎች የሚቆጠሩ የተደራጁ ታጣቂዎች የኢትዮጵያን ድንበር በማቋረጥ በዐሥር መንደሮች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ዘግቧል። ጥቃት ፈጻሚዎቹ በደቡብ ሱዳን የቡማ ወይም ጆንጊሌ ግዛት የሚገኙት የሙርሌ ጎሳ አባላት መሆናቸውንም አትቷል።
በጥቃቱ የተገደሉት ሰዎች ቁጥር 221 መድረሱን የዘገበው ሱዳን ትሪቢዩን 170 የኔዌር ጎሳ አባላት እና 51 የሙርሌ ጎሳ አባላት መገደላቸውን አትቷል።
ለኢትዮጵያ መንግስት ቅርበት ያላቸው መገናኛ ብዙሃን የታጣቂዎቹ ማንነት እንደማይታወቅ እና «መከላከያ ሰራዊት ጭፍጨፋውን የፈጸመው ቡድን ላይ ተከታትሎ አርምጃ እየወሰደ መሆኑን ዘግበዋል።

No comments:

Post a Comment