Saturday, April 30, 2016

የኢትዮጵያ መንግሥት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን ከእስር እንዲለቅ ዩናይትድ ስቴትስ ጥሪ አቀረበች

 


የኢትዮጵያ መንግሥት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን ከእስር እንዲለቅ ዩናይትድ ስቴትስ ጥሪ አቀረበች
‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Journalism‬ ‪#‎FreethePress‬ ‪#‎WoubishetTaye‬
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እ.አ.አ. ሰኔ 19, 2011 በመንግስት ባለሥልጣናት ታሰረ። ውብሸት በአማርኛ ቋንቋ የሚሰራጨው የአውራምባው ታይምስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ነበር።
አንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት እንደገለጸው ውብሸት ከመታሰሩ በፊት ገዢው ፓርቲ የሚተች ጽሁፍ አቅርቦ ነበር። ውብሸት አዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ዩኒቲ ኮሌጅ ነው የጋዜጠኝነት ሞያውን የጀመረው። ከዚያም አሁን በታገደው ሃዳር በተባለ ነፃ ሳምንታዊ ጋዜጣ ሞያውን ቀጠለ። እ.አ.አ. ጥር 19, 2012 በአዲስ አበባ የሚገኝ ፍርድ ቤት በአሸባሪነትና እና ለአሸባሪነት ገንዘብ በመከፈል ወንጀለኛ ተባለ። ከዚያም 14 አመታት እስራት ተፈርዶበት በአሁኑ ወቅት በዝዋይ ማረምያ ቤት ይገኛል። የጤንነቱ ጉዳይም አስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ መንግስት ውብሸት ታዬን እንዲለቅ እንጠይቃለን። የሽብር ህጉም በነጻ ሃሳብን ለመግለጽ እንቅፋት እንዳይሆና የጋዜጠኞችን ስራ ለማጣጣል መንግስቱ እንዳይጠቀምበት ጥሪ እናቀርባለን።
Read More : http://amharic.voanews.com/a/woubishet-taye-highlighted-in-state-department-campaign-call-to-free-press-/3308942.html

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እ.አ.አ. ሰኔ 19, 2011 በመንግስት ባለሥልጣናት ታሰረ

No comments:

Post a Comment