Thursday, April 28, 2016

በአዲስ አበባ ባለ5 ፎቅ ህንጻ ተደረመሰ

5

addis ababa
በአዲስ አበባ በተለምዶው ሠሚት የሚባለው የአዲስ አበባ ሰፈር የደረሰው ይኸው የህንፃ መደርመስ ዛሬ ንጋት ላይ ያጋጠመ ሲሆን በወቅቱ በፎቁ ላይ ሰው ስላልነበረ የሰው ህይወት ተርፏል ሲል አድማስ ራድዮ ዘገበ::
አድማስ ራድዮ እንደዘገበው ፎቁ የተጀመረ ፎቅ ነው። ከታች ግን ሁለት ባንኮች ባላለቀው ፎቅ ስር ሆነው አገልግሎት ይሰጡ ነበር። በአገር ቤት በያንዳንዱ ያላለቀ ፎቅ ሥር ባንኮች እንዳሉ ይታወቃል።
እንደራዲዮው ዘገባ የባንኮቹ የጥበቃ ሰራተኞች ህንፃው ከመድርመሱ በፊት ከባድ ድምፅ በመስማታቸው ከአደጋው ሊያመልጡ ችለዋል። በአዲስ አበባ የሚሰሩ ህንጻዎች ጥራት ጉዳይና ባላለቁ ህንጻዎች ውስጥ ሥራ መጀመር ሁልጊዜም ትችት ሲቀርብበት እንደነበር የሚታወስ ነው።

No comments:

Post a Comment