Monday, July 18, 2016

በጎንደር‬ ዘመናዊና ትልቅ ሆቴሉ ይጠቃል የተባለው በረከት ስሞኦን ጠላቶቹ ተነስተውበታል ተባለ::


በጎደር‬ በተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ ዘመናዊና ትልቅ ሆቴሉ ይጠቃል የተባለው በረከት ስሞኦን በወያኔ ውስጥ ያሉት ጠላቶቹ ተነስተውበታል ተባለ:: በረከት የነ ደብረጽዮንን ስብስብ ከሚቃወሙትና የመቀሌ ቡድን ከሚባሉት ጋር በማበሩ የደብረጽዮን ደጋፊው የሆነው የጸጥታው የበላዩ ሀላፊ የጌታቸው አሰፋ ጥቃት ሲደርስበት የቆየ መሆኑ ይታወቃል ያሉ ክፍሎች ትውልደ ኤርትራው በረከት የአዜብ መስፍንም አጋር መሆኑ ብዙም አልጠቀመውም ብለዋል ።
ለጎንደር ሕዝብ ተቃውሞ ምክንያት ሆኗል እየተባለ ያለው በረከት በብአዴን ውስጥ እየተጠናከረ የመጣውን ጸረ ወያኔ አቅዋምም ሊቆጣጠር አልቻለም እየተባለ ነው ። አንዳንድ የብአዴን አመራር አባሎች በጸረ ወያኔው ትግል ከኢሕአፓ ጋር መገናኘት ሞክረዋል ሲል ኢንዲያን ኦሽን ኒውስ ሌተር ቀደም ብሎ ስላቀረበው መረጃ ማረጋገጫ ባይገኝም በርከት ያሉ የብአዴን አባላት ወያኔ አማራው ላይ የሚያደርሰውን ጥቃትና ብአዴንንም ነጻነት ማሳጣቱን እየተቃወሙ መምጣቻው ሀቅ ነው ተብሏል ።

No comments:

Post a Comment