Monday, July 18, 2016

ተቃውሞ እና የሹፌሮች ስራ ማቆም አድማ በምእራብ ሸዋ ተካሄደ:: ፀረ-ሕዝብ መንግስታዊ ሽብርተኝነት ቀጥሏል::


 ተቃውሞ እና የሹፌሮች ስራ ማቆም አድማ በምእራብ ሸዋ ተካሄደ:: ፀረ-ሕዝብ መንግስታዊ ሽብርተኝነት ቀጥሏል:: 
– በምእራብ ሸዋ ጀልዱ እና ጊንጪ ተቃውሞና የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችና የሚኒባስ የስራ ማቆም አድማ የተደረገ ሲሆን በጀልዱ ከተማ በርካቶች በወያኔ አግኣዚ ጥይቶች ተመተው ክፉኛ መቁሰላቸው ታውቋል::ይኸው ተቃውሞ በግንደበረት እና አጎራባች አከባቢዎች የተደረገ ሲሆን ሕዝቡ መንገድ በመዝጋት ተቃውሞ መግለጹ ታውቋል::በጊንጪ እና በአከባቢው ከተሞች የአውቶብስ መናኸሪያዎች የሹፌሮችን አድማ ተከትሎ በርካቶች አውቶብሶችን አጥተው የተመለሱ ሲሆን በምእራብ ሸዋ የሚገኙ አውቶብስ መናኽሪያዎች በተሳፋሪዎች ተጨናንቀው ተስተውለዋል::ምንሊክ ሳልሳዊ
በጀልዱ ወረዳ እና በአከባቢው ከተሞች በተካሄደ ተቃውሞ በጎጆ ከተማ በጥይት ተመትተው የቆሰሉ
1ኛ- ብርሃኑ ጫላ – ሸንኩቱ ከተማ ታሶ አከባቢ
2. በይሳ ቀልቤሳ – በቾ
3. አቡሽ ነጋሳ – ጎጆ
4. ደጀኔ ቡልቻ በቾ
5. ሲሳይ ደበላ – ጎጆ
6. ባይሳ ኦልጋ – ጎጆ ሲሆኑ በሸንኩቴ ከተማ ማምሻውን ድረስ ተቃውሞ የቀጠለ ሲሆን መንገዶች በሙሉ ተዘግተዋል:: ፀረ-ሕዝብ መንግስታዊ ሽብርተኝነት ቀጥሏል::
Minilik Salsawi's photo.
Minilik Salsawi's photo.
Minilik Salsawi's photo.
Minilik Salsawi's photo.
Minilik Salsawi's photo.
 

No comments:

Post a Comment