Friday, May 20, 2016

በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከትናንት ጀምሮ በፌደራል ፖሊስ እየተቀጠቀጡ ነው – አንዱን ፖሊስ ከህንጻ ገፍትረው ጣሉት (ፎቶዎች ይዘናል)


  • 1002
     
    Share
13087681_10102296231705053_4077424415859432752_n13221028_10102296231635193_759698516884747726_n
13254093_10102296231320823_8172214177964234618_n
(ዘ-ሐበሻ) ተማሪዎች በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ የመብት ጥያቄ ማንሳታቸውን ተከትሎ የፌደራል ፖሊሶች በተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ድብደባ መፈጸማቸውንና ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስም በተማሪዎቹ ላይ የሚደርሰው ጉዳት ማየሉ ተዘገበ::
ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ያነሱትን ተማሪዎች ፖሊስ ዛሬ ጠዋት ድረስ መኝታ ክፍላቸው ውስጥ በመግባት እንደቀጠቀጠና ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰ የሚገልጹት የዘ-ሐበሻ የዜና ምንጮች በተለይም አብዛኞቹ ተማሪዎች መፈነካከታቸውና ከ15 የማያንሱ ተማሪዎች በከፍተኛ ጉዳት ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል::
13230103_10102296234803843_6114860639105908605_n
ተማሪዎቹ ከመኝታ ክፍላቸው እንዳይወጡ ህንጻዎች በሙሉ በፌደራል ፖሊሶች እንደተከበበ የሚገልጹት ምንጮች ከሚደርስባቸው ድብደባ ለማምለጥ ሲሞክሩም አንዱን ፌደራል ፖሊስ ከህንፃ ላይ ገፍትረው እንደጣሉትና ፖሊሱም ጉዳት እንደደረሰበት ገልጸዋል::
ፌደራል ፖሊሶቹ በተማሪዎቹ ላይ የሚፈጽሟቸው ግፎች ከድብደባ በላይ አንዳንዱን ተማሪ በጠራራ ጸሀይ ላይ እያንበረከኩ ጸሐይ በማስደብድበ በግሩፕ እንደሚገርፉቸው ያስታወቁት ምንጮቻችን በሴት ተማሪዎች ላይ ሳይቀር ከትናንት ጀምሮ እየተፈጸመ ያለው ድብደባ የሚዘገንን ነው ብለዋል::
በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ ውጥረቱ እንዳየለ ሲሆን ዘ-ሐበሻ እየተከታተለች ጉዳዩን ለመዘገብ ትሞክራለች::

ፎቶዎቹን ያሰባሰብናቸው ከሶሻል ሚዲያዎች ነው::

No comments:

Post a Comment