Sunday, May 22, 2016

በወልቃይት ቃብቲያ በህዝቡና በትግራይ ልዩ ሃይል ፍጥጫው ዛሬ ተጠናክሯል። ከ15 ሺህ በላይ ህዝብ ስብሰባ ወጥቷል።

በወልቃይት ቃብቲያ በህዝቡና በትግራይ ልዩ ሃይል ፍጥጫው ዛሬ ተጠናክሯል። ከ15ሺህ በላይ ህዝብ ስብሰባ ወጥቷል። የትግራይ ልዩ ሃይል ስብሰባው ለመበተን ሞክሮ አልተሳካለትም። በህዝቡ ሃይል አፈግፍጓል። የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ‪
በ14/9/08 የቃብቲያ ህዝብ ያካሄደዉ ስብሰባ ከ15000 በላይ የወልቀቃይት አማራ ማንነት ደጋፊወች በድጋሚ የትግራይ ክልል የአማራ ማንነታ ያለአንዳች ቅደመ ሁኔታ ተቀብሎ አስተዳ ደሩ በወልቀቃይት አማራወችና በአማራ መንግስት ስር እነዲሆን ጥያቄዉን ከዛሪ ጀምሮ መቀበል ያለበት ህጋዊ የሆነ የፊደራል መንገስት ከትግራይ ተወላጆች ተጽእኖ ራሱን የቻለ የፊደራል ስብጥር ያለዉ የመንግስት አካል ካልሆነ የትግራይ አስተዳደር ከክልላችንና ከቦታችን ይልቀቅ፣ ህገ መንግስቱን መሰረት አድርገን የጠየቅነዉ ጥያቄ በአስቸኮይ መልስ ይሰጠን በማለት ድምፁን ሲያሰማ ውሏል። ምንም እንኮ በዛሪዉ ስብሰባ ከሁመራ ባህከር ማይካደረራ ከወልቃይት ጠገዴ ከ50000 ሺ በላይ ሰዉ ወደስብሰባዉ የተመመ ቢሆንም በሁለቱም አቅጣቻ ኬላወች የትግራይ ልዩ ሃይል ህዝቡን አግቶ ቢዉልም ከ15000 በላይ የሚሆን ጀግናዉ የቃብቲያ ህዝብ ስብሰባዉን ተካፍሎ አቆሙን በግልጽ አስቀምጦል።
⏯የትግራይ ክልል አማራን አይመራም ህገ- መንግስታዊ መብታችን ይከበር !!
⏯ወልቃይት የአማራ መነሻና ምድራዊ ገነት ናት !!
⏯የህዝቡን መሰረታዊ ፍላጎት ያሞላ የወልቃይት አማራወች መብት ይከበር
⏯ድል ለቃብቲያ ሰላማዊ ኮንፍረንስና ምስጋና ለጀግናዉ የቃብቲያ ህዝበ !!

No comments:

Post a Comment