Sunday, May 29, 2016

ቴአትርና ፊልም አሁንም ባርነት ላይ ናቸው፡፡ ክ/ሀገር ቴአትር ማሳየት አይታሰብም፡፡


ግንቦት 20፤ ለኪነ-ጥበቡ አበረከተየሚባለው ነገር ቅድመ ምርመራን ማስቀረቱቢሆንም ቴአትርና ፊልምን ግን ከደርግ ሳንሱርአልተላቀቁም፡፡ ለምሳሌ ሥነ ጽሑፍ፣ ስዕልናሙዚቃ ቅድመ ምርመራ አይካሄድባቸውም፤ቀድመው አይታዩም፤ አይመረመሩም፡፡ ይሄመጽሐፍንም ጋዜጣንም ጭምር ነው፡፡ ፊልምናቴአትር ግን ይገመገማሉ፡፡
በደርግ ጊዜ የነበረውአሰራር በፊልምና ቴአትር ላይ እስካሁን ቀጥሏል፡፡ለምሳሌ ቴአትር ለማሳየት ባህልና ቱሪዝምፈቃድ ካልሰጠሽ ቴአትርሽ አይታይም፡፡ ባህልናቱሪዝም ፈቃድ ካልፃፈ፣ ክ/ሀገር ሄደሽ ቴአትር ማሳየት አይታሰብም፡፡ ፊልምሽ ሲኒማ ቤት ለመታየት መጀመሪያ መገምገም አለበት፡፡በአንቺ ስራ ላይ የባህልና ቱሪዝም ሰዎች(ገምጋሚዎቹ) “ይህን ነገር ጨምር፤ ይህንን ነገርአውጣ” የማለት መብት አላቸው፡፡ እስካሁን በግምገማ ምክንያት የታገዱ ምን ምን የመሳሰሉ ቴአትሮችና ፊልሞች አሉ፡፡
“ወይ አዲስ አበባ” የተባለ የጌትነት እንየው ቴአትር በግምገማ ምክንያት ከታገዱት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው፡፡ ይህ ቴአትር ተገምግሞ ታግዷል፡፡ ይህ የሆነው ሊከፈት ለህዝቡ መጥሪያ ከተላከ በኋላ ነው፡፡ ኢህአዴግ ወይም ግንቦት 20፤ ፊልምና ቴአትርን ገና ነፃ አላወጣቸውም፡፡ በቃ ቴአትርና ፊልም አሁንም ባርነት ላይ ናቸው፡፡

No comments:

Post a Comment