Sunday, May 22, 2016

መቀለ በቅዳሜና እሁድ በግዳጅ ሠልፍ ተንጣ ዋለች !! – አስገደ ገብረስላሴ

 የመቀሌ ህዝብ ፣የባጃጅ ፣ የታክሥ ሽፈሮችና በለንብረቶች የተቃውሞ አድማ በግልፅ ታዬ !!
የተግራይ ህዝብ ለካቲት 11 ህወሃት ትጥቅ ትግል የጀመረበትና የጉንበት 20 ደርግ ተሸሮ የተወገደበት የድል በአላት ለማክበር ገና ጊዜው ሣይደርሥ በሽኮላና በጉጉት በመጠባበቅ በራሡ ተነሣሽነት ማንም ሣያንቀሣቅሠው ግብዣና ሞፎከር ያዛጋጅ ነበር ። በተለይ ደግሞ ለካቲት 11 የህወሓት የመሥረታ በአል በትጥቅ ትግል ጊዜ ከማንም አማልክት በላይ በማምለክ በቤቱና ህዝብ በተሠበሠበበት እጅግ ቡዙ ወጭ በማድረግ ግብዣ አድርጎ የአድባራት ታቦት በሠልፍ ወጥተው ከማክበር አልፈው ሁሉ ወላጅ ከ15 አመት እድሜ በላይ ከዛ በታችም ህፃናት ፣ለብሥ አልብሦ ወደትግል ሜዳ ለመሥዋእት ልብሥ አልብሦ ፣አሥፈለጊ ሥንቅ ሠጥቶ በጭፈራ፣በእልልታይሸኝ ነበር ።
ለጉንበት 20የድል በአልም በመጀመሪያዎቹ አመታት በደሥታ ያከብር ነበር ።
ያሁሉ የሚያደርጉት የነበረ ገዥዎች ያደርሡበት የነበረ ግፍና ጭቆና አሥወግዶ ረሀብ ሥደት ጠፍቶ ፣ሠላም ፍትህ ነፃነት ፣ የህግ የበላይነት ፣ የዲሞክራሢና የዜጎች ሠብአዊ መብቶች መከበር ተረጋግጦ ፣ዲሞክራሢያዊ ህዝባዊ መንግሥት በመመሥረት ልማት ተሥፋፍቶ ፣ የበለፀገች ኢትዮጱያ ለማየት ነበር ።
ያሁሉ የተመኜው ነገር ግን ሣይሆን ቀርቶ የህወሃት ኢህአደግ ሥርአት ከነዛ በሥብሠውና ፣ላሽቀው የወደቁ ሥርአቶች የባሠ የሠለጠነ አንባገነን ፣ወደ ፋሸዝም ጎደና ያመራና ፣በተግባርም ከደርግ በባሠ የሠለጠነ ፈሽሽት ሆኖ በመገኜቱ ፣የኢትዮጱያ ህዝቦች የተመኙትን ሁሉ ውሃ ዘግነው ቀሩ!!! ።
በተለይ ደግሞ የትግራይ ህዝብ በቅርብ የህወሃት አጋር ሆኖ ለ17 አመት ሙሉ ሁሉም አይነት ሀብቱ ፣ልጆቹ አማጡጦ የጨረሠ ህዝብ በመሆኑ ፣ የተገባለት ቃል 100%ሥለካዱት ፣ በአሁኑ ጊዜ ለህወሃት መሪዎችና አጋራቻቸው ፓርቲዎች ከነመዋቅራቸው ከአእምረው አውጥቶ ተፍቶዋቸው ይታል ።
ለዚሁ አንድ መሥረጃ የትላንተና የታክሥ ፣የባጃጅና የታክሥ የግዳጅ ጉንበት 20 አሥመልክቶ ሠልፍ ፣የታየው ተቀውሞ ድሮ ከአንድ በላይ ባነዴራ ያደርጉ የነበረ የዛሬው ሠልፍ አለፎ አልፎ ባንዴራ ያደረጉ ቢኖሩም በየመንገዱ ጥለውታል ፣ ቡዙ ታክሢዎች ደግሞ ባዶ ትላልቅ ሃይላንድ ቁልቁል አፉ በእንጨት ሠክተው አንደበንዴራ እያውለበለቡ ታይተዋል ። እነዚህ ባለታክሢዎች ተገደው በተሠበሠቡበት በጉሩፕ በጉሩፕ ሇነው ከነዚህ ሠወች መቸ ነው እምንላቀቀው እያሉም ይናገራሉ ።
እነዚህ ባለታክሢዎችና በለባጃጆች ከ6 ሠአት እሥከ 12 ሠአት ማታ በግዳጅ ሠልፍ ሥለታሠሩ የመቀሌ ታክሥ ተገልጋይ ህብረተሠብ ፣ተመሪዎች ፣ ሠራተኞች ምሬታቸውነ ይገልፁ ነበሩ ። በኢኮኖ ሚ አይን ሢታይም ባለታክሢዎች የከሠሩት እያሠሉ ሢናገሩ ከሁለት ሚሊየን ብር በላይ እንደከሠሩ ተናረለዋል ።
በሌላ በኩሉ ለዛሬ ቅዳሜ ጥዋት የመቀሌና የአጓራባች ቀበሌዎች ጉንበት 20 አሥመልክቶ በግድ ሠልፍ እንዲወጣ ታዞ የመነግሥት ሠራተኛ በከፊል ፣ የኤፈርት ሠራተኞችም በከፊሌ ፣ የቀበሌ ተላላኪ ሤቶችና ተጠቃሚዎች ፣የሀገር መከላከያ ሠራዊት ፣ ፖሊሥ ፣ እንዲሁም ተማሪዎች ያልመጣ የአመት መጣቃለያ ፈተና አትፈተኑም በሚል በማሥፈራራት የተሠለፉ በሥተቀር የመቀሌ ህዝብ ሠልፍ አልወጣም ። ይህ የሚያሣዬው ህወሃት ኢህአደግ ምን ያ
ህል ከህዝብ ልብና አእምሮ ወጥቶና ርቆ እንዳለ ያሣያል ።
ግን እነዚህ ሠዎች ለምን ካለፉት ሠርአቶችና ፣ የአካባቢያቸው አንባገነኖች መንግሥታት አዋዳደቅ አይማሩም ?እነዚህ ሠዎች መንግሥታት ወታደር መድፍ ምሣይል ፣ሚግ ተዋጊ ፣ መንጋ ሥለላ ቢሠበሥቡ ፣ በያረዱ ፣ቢ ሠቅሉ ፣ቢያሥሩ ፣ ህዝብ እንደማይሸነፍ ያውቃሉ ። ለምን አይማሩም ??????

No comments:

Post a Comment