Sunday, October 29, 2017

የትምክህትና የጥበት ልብ አውልቅ ፕሮፓጋንዳ



  
By ሳተናውOctober 29, 2017 11:17
    
በታደሰ ሻንቆ
በተራው ሰው ደረጃም ሆነ በኢሕአዴግ ግንባርና መንግሥት ዘንድ የሚነፍሰው የትምክህትና የጥበት አጠቃቀም፣ በአንድ ፈርጁ የህሊና ድህነትን ለአመል የመቀነስ ጥቅም እንኳ መስጠት ያልቻለ፣ ግልብ፣ ከግልብም ዲዳ ሆኗል፡፡ በሌላ ፈርጁ ደግሞ ማኅበረሰባዊ ግንኙነትን ለማቀራረብም ሆነ ችግሮችን ለመፍታት ከማገዝ ፈንታ እየጓጎጠ የሚያቆስል ጨፍራራ ነገር ሆኗል፡፡ የጽንሰ ሐሳቦች መላሸቅ ውጤት የሆነው በተራ ሰው አካባቢ የምናገኘው አጠቃቀም፣ ትምክህተኛነትን ከአማራነት ጋር አንድ እስከማድረግ የነተበ፣ በየብሔረሰብ ቋንቋና ባህል መገልገልን ሁሉ በጥበትነት እስከ መገመት ድረስ የቀለለ ነው፡፡ በኢሕአዴግ ሰዎችና በፕሮፓጋንዳ አናፋሾች ዘንድ የሚታየውም የጥበት አጠቃቀም እንዲሁ የአስተሳሰብ ብልሽትን ከመብት ጥያቄና ከማኅበረሰባዊ ማንነት አጥርቶ የመለየት ችግር ያለበት ነው፡፡ ከዚያም አልፎ ከኢሕአዴግ ያልገጠመ አመለካከትን ወይ ጥበት ነው ወይ ትምክህት ነው ብሎ እስከመፈረጅ መፈናፈኛ ማሳጣት ተዘውትሯል፡፡ ለሕዝብ ቀለብነት በሚረጨው ፕሮፓጋንዳ ውስጥ ያለውን የይዘት ችግር ማሳየት ዞሮ ዞሮ ከመለኪያና ከቡና ስኒ ጋር የሚነፍሰውን እሳቤ ለማሳየትም ይጠቅማልና ለአዳባባይ ፍጆታ በሚረጨው ላይ እናተኩር፡፡
ስለትምክህትና ጥበት ዛሬ እየተባለ ያለው ነገር የዕውናዊነት አቅሙ የተውለቀለቀና ብልሽትን ማደናገሪያ ሆኖ እስከማገልገል እየሠራ ነው፡፡ የኢሕአዴግ የትንተና መጽሔት አዲስ ራዕይ (በ2009 የየካቲትና መጋቢት ዕትም፣ ገጽ 8) ላይ ‹‹በአሁኑ ጊዜ የትምክህት አመለካከት ከሥልጣን የተወገደው መደብ አመለካከት እንጂ ሥልጣን ላይ ያለ ገዥ አመለካከት አይደለም፡፡ የአሁኖቹ የትምክህት ኃይሎች አንድም በመሠረቱ ያለፈው ገዥ መደብ ቅሪቶች ወይም አዳዲሶቹ ጥገኞችና የእነሱ ጠበቆች ናቸው፡፡ ስለሆነም በወሳኝ መልኩ የተሸነፈ አመለካከት ነው . . . [ለዚህም] ዋነኛ ምክንያቱ . . . ማኅበራዊ መሠረቴ ነው ብሎ በሚያስበው በሰፊው የአማራ ሕዝብ ዘንድ የተጠላና የተሸነፈ ስለሆነ ነው፤›› ይላል፡፡ በዚያው ገጽ ላይ፣ የትምክህት ዋነኛ ይዘቱ የራስን ብሔር የበላይነት ማስፈን እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ዝቅ ብሎ (ገጽ 9 ላይ) ደግሞ ‹‹…የትምክህተኛው የሁልጊዜ ህልሙ… በአንድነት ስም የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦችን መጠቅለል ነው፤›› ተብሏል፡፡ የተሸነፈ የተባለው ትምክህት ስለእውነት ዛሬ የሚብከነከነው ብሔር ብሔረሰቦችን ጠቅልሎ በአማራ የበላይነት ሥር የማስገባት ፍላጎት ነው? እንደዚህ ያለ አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትን ችግሮች ባህርይ ለይቶ ለመፍታት ይረዳል? በአገራችን ውስጥ ያለው ኢትዮጵያን ከመበታተን የማትረፍ ፍላጎት ኢዴሞክራሲያዊ ሥልት እስከ መጠቀም (እስከ ደም ጠብታ የመሄድ) ጫፍ አለው፡፡ እዚህ ጫፍ ውስጥ የተገኘ ሁሉ ግን በደፈናው ትምክህተኛ ሊባል አይችልም፡፡ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ብቻውን ሊያናጭና ዘራፍ ሊያሰኝም ይችላል፡፡ ልክ እንደዚሁ ተነጣዮችን የጥበት የተስፈነጠረ ክፍል አድርጎ በመለየት ፈንታ ‹‹የጠባቦች ህልም የእኛ ነው የሚሉትን ሕዝብ ለብቻ ገንጥለው… የቡድን ፍላጎቶችን በአቋራጭ ማረጋገጥ›› አድርጎ ማጠቃለልም ትልቅ ስህተት ነው (ገጽ 9፣ ሰረዝ የተጨመረ)፡፡
ኢሕአዴግ በውስጡ ያለውን የጠባብነትንና የትምክህትን ጣጣ ለአባል ድርጅቶቹ ሲደለድል፣ ‹‹ብአዴን ትምክህተኝነትን ሲዋጋ ሕወሓት፣ ኦሕዴድና ደኢሕዴን ጠባብነትን ሲዋጉ …›› ይላል (ገጽ 45)፡፡ ይህንን ድልድል ቀደም ብለን ከጠቀስናቸው ‹‹የትንታኔ›› ሐረጎች ጋር እናገናዝበው፡፡ ‹‹ትምክህት የተወገደ መደብ  አመለካካት፣ ዛሬ ሥልጣን ላይ የሌለ አመለካከት፣ የቀድሞ ገዥዎች ቅሪቶች/ጠበቆች አመለካከት›› አለዚያም ‹‹የአዲሶቹ ጥገኞች አመለካከት›› የሚሉትን ሐረጎች ተመርኩዘን ትምክህት ለምን ከብአዴን ጋር እንደተያያዘ ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ የቀድሞ ገዥዎች ከአማራነት የበቀሉ፣ የዛሬው ትምክህተኛነትም የእነሱው ርዝራዥ ወይም ጠበቃ የመሆን ችግር ተደርጎ መቆጠሩን የሚያመለክት ነው፡፡ እንደዚያ ከሆነና ከገዥነት ትምክህት ከፈለቀ፣ የቀድሞው የአማራ ገዥነት ትምክህትን እንዳፈለቀ ሁሉ ስለምን የዛሬው የሕወሓት፣ የኦሕዴድም ሆነ የደኢሕዴን ገዥነት ትምክህትን አላመነጨም? ከእነዚህኞቹ አካባቢ የሚከሰት እብሪት ስለምን ከጥበት ጋር ተያይዞ ይታያል? የሚል ጥያቄ ብናነሳ መልስ ይቸግረናል፡፡ እኛ ቢቸግረንም የኢሕአዴግ ‹‹የትንተና›› መጽሔት መልስ አለው፡፡ ‹‹በዱሮ ጊዜ ትምክህት በሥልጣን ላይ ከነበሩ ገዥዎች የሚፈልቅ አስተሳሰብ ነበር፡፡ ጠባብነት ደግሞ ራሱን ለሥልጣን በተስፈኝነት ከሚያጨው ንዑስ ባለሀብት የሚመነጭ ነበር፡፡ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት ጀምረን እነዚህ ሁለት ምንጮችን ካደረቅን በኋላ እነዚህ አመለካከቶች ከጥገኛ ኃይል የሚመነጩበት ሁኔታ እንዳለ ታይቷል›› (ሰርዝ የተጨመረ፡ ገጽ 38)፡፡
በዚህ አባባል መሠረት የትምክህት ከገዥነት መፍለቅ፣ የጥበትም ወደ ገዥነት ከመንጠራራት መፍለቅ የዱሮ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ስለምን? ዴሞክራሲ ‹‹በመጀመሩ›› ምንጫቸው ‹‹ደርቋል››፡፡ እንግዲህ በእኛ ‹‹ዴሞክራሲ›› ገዥነትና ተገዥነት የለም መባሉ ነው፡፡ እናም ለዛሬ ጥበትና እብሪት ሌላ ምንጭ ተፈልጎ ተገኘለት ‹‹ጥገኝነት›› የሚባል፡፡ ለመሆኑ ጥገኝነት መናፍስት ነገር ካልሆነ በቀር፣ ከላይ እስከ ታች ሥልጣን ላይ ተቀምጦ በጎሰኛ በዳይነትና መጥማጭነት እየተንፈላሰሰ ሲቅለጠለጥ የታዘብነው ክፍል ገዥ ካልተባለ ምን ሊባል ነው? ደግሞስ የኢሕአዴግ አስተዳደር የብሔር ጭቆና የሌለበት ዴሞክራሲያዊ እኩልነትን ለሕዝቦች አጎናፅፎ ከሆነ በመወደስ ፈንታ፣ ስለምን እያደገ በመጣ ቅዋሜና በኢሕአዴጋዊ የበላይ ገዥነት ይነዘነዛል? ኢሕአዴግ ጎሽ የተባለው ያገኘው በልማት ረገድ እንጂ በአገዛዙ አይደለም፡፡
ሌላም መልስ የሚሻ ጥያቄ አለ፡፡ ብአዴን እንደነ ኦሕዴድ በብሔርተኝነት አዕምሮ የታሰሰ፣ ብሔርተኛ ዓላማ ያነገበ፣ በብሔር የተደራጀና የአማራ ክልልን የሚገዛ እንደ መሆኑ እንደነሱ በጥበት ችግር ስለምን አይታማም? ስለምን ከትምክህት ችግር ጋር ይዛመዳል? በዱሮው ገዥነት ርዝራዥ አስተሳሰብና ባህል የመጎተት ፈተናና ትግል ስላለበት ነው ይባል ይሆን? እንዲያ ከተባለ ደግሞ ስለአማራ የገዥነት ዘመን ሲወራ የበላይነት ሥፍራውን ስለመያዙ እንጂ፣ በገዥነቱ ውስጥማ ከሌላ ብሔረሰብ የበቀሉም ነበሩበት፡፡ በገዥነት ውስጥ ከላይና ከሥር መሆን ሊኖር፣ ከሥር የነበረ ወደ ላይ ሊወጣ፣ ከላይ የነበረ ከሥር ሊገባ ይችላል፡፡ የትግሬ መሳፍንትን የቅርብ ጊዜ የቅሬታ ምክንያት ብናስታውስ፣ በዮሐንስ አራተኛ የተዘረጋውን የትግራዊ የበላይ ገዥነት ምኒልክ ጣልቃ ገብቶ ሟቋረጡ ነበር፡፡ ይህ ታሪክ ተራ ገበሬ ድረስ የገባ የቅሬታ አሻራ ትቶ አልፏል፡፡ ከዚህም ባሻገር በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከአማራ ሌላ የትግሬ፣ የአገው፣ የኦሮሞ መሳፍንታትም አነሰም በዛ የበላይ ገዥነት ድርሻን በተለያየ ጊዜ ተቃምሰዋል፡፡ በዱሮ ገዥነት ጀርባ መመካት አማራን ከሳበ፣ ሌላውንም የማይጎትትበት ምክንያት አይኖርም፡፡ ለዚህም አብነት ባለንበት የኢሕአዴግ ዘመን ውስጥ እንኳ ብሔርተኛነትን ከገዥነት ታሪክ ኩራት ጋር አጎዳኝተው የተረኩ የጽሑፍ እማኞች አንድ ሁለት ብሎ መቁጠር ይቻላል፡፡ ለዚህ ጽሑፍ የተጠቀምኩበት አዲስ ራዕይ መጽሔት (የካቲት መጋቢት 2009 ዕትም) ራሱ ሳያውቀው በኢሕአዴግ ውስጥ ስላለና ከድሮ ገዥነት ጋር ያልተያያዘ ትምክህትም ፍንጭ ሰጥቶናል፡፡ በኢሕአዴግ ፕሮፓጋንዳ የተለመደውን ጥበትንና ትምክህትን አነፃፅሮ መመልከትን መጽሔቱም የሚከተል ቢሆንም፣ ገጽ 9 ላይ የጠባብነት ሌላ መገለጫ ብሎ ያሠፈረው ‹‹ራስን የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ብቸኛ ባለቤትና ጠባቂ አድርጎ ማሰብና ሌሎችን በጥርጣሬ ዓይን የማየት አዝማሚያ›› በቅጡ ላስተዋለው የሚያንፀባርቀው ጎጇዊ ጥበትን ሳይሆን የትምክህትን ጥበት ነው (ሰረዝ የተጨመረ)፡፡
በሌላ በኩል በ2008 ዓ.ም. በአማራ ክልል ውስጥ የታዩ ጣጣዎችንም የትምክሀት ውጤት አድርጎ ለመግለጽ መጣደፍ ለስህተት መጣደፍ ነው፡፡ ወደ ትግራይ ያለፈ መሬት አለኝ የሚለው በአማራ ክልል ውስጥ የተነሳው ጥያቄ በሌሎች ክልሎች መካከል ከተነሳው ጋር የባህርይ ልዩነት የለውም፡፡ ቅማንቶች ከአማራነት የተለየ ማንነት አለን ሲሉም የተነሳው ‹‹አንድ ነን፣ ለምን እንከፋፈላለን፤›› የሚለው ቅማንቶችን ጭምር ያካተተ ቅዋሜም (የነበረውን ትምክህታዊ የንቀት ታሪክ ወደ ጎን አድርገን ስንመለከተው) ከእኛ መዳፍ ውስጥ ምን ቆርጧችሁ ትወጣለችሁ በሚል ማን አህሎኝነት ፈጽሞ የማይብራራ፣ ሥልጤዎችና ወለኔዎች ከጉራጌ ማኅበረሰብ እንለያለን ባሉ ጊዜ ከተነሳባቸው ቅዋሜ ጋር በብዙ ነገሩ ተመሳሳይ ነው፡፡ በ2008 ዓ.ም. ቁጣ ጊዜ በትግራዊ ሰዎች ላይ የተከሰተውን መተናኮልም በጠቀስነው አዲስ ራዕይ ውስጥ እንደሠፈረው ከትምክህታዊ ጭፍን ጥላቻ የተወለደ አድርጎ ማቅረብም እውነተኛ ምክንያቱን ለይቶ መፍትሔ ለመፈለግ የማይጠቅም ነው፡፡ የመሬት ጉዳይ የታከለበት ከመሆኑ ባለፈ፣ በትግራዊነት ላይ የተዛመተው ድፍርስ ስሜት በሌሎች አካባቢዎች ውስጥ ከተዛመተው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ የጋራ መነሻውም ሕወሓት መራሽ ገዥነት ውስጥ እንገኛለን ከሚል ማዕዘን ትግራዊ ሰዎችን በሥርዓቱ የበለጠ ተጠቃሚና የሥርዓቱ ጠባቂ አድርጎ መመልከት ነው፡፡ መፍትሔው የሚገኘውም ለምን ትግራዊ ላይ እንዲህ ያለ አመለካከት ወደቀ? ይህስ እንደምን ይገፈፋል? የሚሉ ጥያቄዎችን በትክክል ከመመለስ ነው፡፡ በትምክህት ማሳበቡ ረብ የለሽ መሆኑን ለማጤን ትምክህት ተሸናፊ ባልነበረበት በአፄ ኃይለ ሥላሴና በደርግ ጊዜ አማራና ትግሬ በጎንደርና በሌሎቹም የአማራ አካባቢዎች ምን ያህል ተላልሶ ይኖር እንደነበር ማስታወስ ነው፡፡ እስካሁን የጠቃቀስናቸው ነጥቦች፣ ሁሉ ነገር በትምክህትና በጥበት ውስጥ ሲሰነቀር እንደማይችል ለመገንዘብ የሚያስችሉ ይመስለኛል፡፡ ትምክህትና ጥበት እንደ ዓይጥና ድመት የሚጠፋፉ ነገሮች እንዳልሆኑ ሁሉ ጥላቻና በቀልም አብረዋቸው የተፈጠሩ ነገሮች አይደሉም፡፡ ትምክህትና ጥበት ጥላቻና በቀልን የሚታጠቁት መተነኳኮልን ሲመገቡ ነው፡፡ የሥልጣን ተዛነፍ፣ ሀብት የማካበት እሽቅድምድምና ተቀደምን/ተዘረፍን ባይነት ባለበት ቅሬታዎችና መብከንከን መኖራቸው አይቀርም፡፡ ቅሬታዎች የትምክህትና የጥበት ስም ቢሰጣቸው አይገቱም፣ ለእነሱ ምንጭ የሆኑት ችግሮችም አይወገዱም፡፡
በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውስጥ በድጎማ ድርሻ ላይ እከሌ ስንት ደረሰው እያሉ ማነፃፀርና ድርሻን ለማሻሻል መጣጣር የተወከሉበትን ተግባር የማካሄድ እንጂ የጥበት ተግባር አይሆንም፡፡ እዚህ/እዚያ ተዳላ የሚል ጥርጣሬን ለማስወገድና ከአጠቃላይ አገራዊ ዕይታ አኳያ መቅደምና መዘግየት ያለባቸውን ሥራዎች ከማስተዋል ጋር የፌዴራል ልማቶችን አካባቢያዊ ድርሻዎች በተመለከተ ጥሩ መግባባት እንዲዳብር ከተፈለገም ከክፍልፋይ ብሔርተኛ ሙሽት መውጣትና ለመተማመን የሚያበቃ የግልጽነትና የፍትሐዊነት ግንኙነት ማጎልበት ነው፡፡
‹‹የጠባብነት/የትምክህት ኃይሎች የመከላከያና የፀጥታ ኃይላችንን ዋና ዒላማ ያደረጉት ከሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች ተነስተው… [ነው]፡፡ የመጀመርያው ጉዳይ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከማንኛው አደጋ የሚጠብቅ… በመሆኑ ይህ ተቋም ካልፈረሰ ወይም ካልተዳከመ ዓላማቸው እንደማይሳካ በመረዳታቸው ነው፡፡ ሌላው መነሻቸው የሠራዊት የከፍተኛ ኃላፊነትን የማመጣጠኑ ሒደት በአንፃራዊነት ረዘም ያለ ጊዜን የሚጠይቅ መሆኑን የሚረዱት እንኳ ቢሆንም፣ አድልኦ እንዳለ በማስመሰል ማቅረብ ቀላልና አቋራጭ መንገድ ብለው ስለሚያስቡ… (የተጠቀሰው መጽሔት፣ ገጽ 23፣ ሰረዝ የተጨመረ)፡፡
ይህን መሳይ ማመካኛ 25 ዓመታት ካለፈው የሥልጣን ቆይታ በኋላ ይዞ መቅረብ በእጅጉ አሳፋሪ ነው!! አንደኛ ነገር ለሐሜት መነሻ የሚሆን ዝንፈት ሲኖር መደረግ ያለበት ሐሜትንና ጥርጣሬን መኮነን ሳይሆን፣ ዝንፈቱን ማስተካከል ነው፡፡ ሁለተኛ ከዝንፈት አልፎ መከላከያና ፀጥታው በአመጣጥም በአመለካከትም ወደ ኢሕአዴግ ያዘመመ መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ በየብሔረተኛ ወገንተኛነት የተሞላ ክልላዊ ታጣቂም ምን ያህል ደም አፋሳሽ ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል እስኪሰቀጥጠን ድረስ ዓይተናል፡፡ ሦስተኛ ሕገ መንግሥቱ የሚለው የተጠቀሱት አውታራት ገለልተኛ ይሁኑ እንጂ ወደ ቡድን ወይም ወደ ፖለቲካ መስመር ያዝምሙ አይልም፡፡ አራተኛ ዛሬም ያለው ጥያቄ ገለልተኛ ሆነው ይታነፁ/ይጠናቀሩ እንጂ ብስል የአመራርና የሙያ ክህሎት ከሥራ ወጪ ሆኖ ይባክን አይደለም፡፡ አምስተኛ ገለልተኛ ይሁኑ የሚለው ጥያቄ የማይረሳ ቁልፍ ጥያቄ የሆነው፣ እመት ነፃነትና እመት ፍትሕ ማጅራታቸው ሳይያዝ፣ ለዘፈቀዳዊ የጉልበት ሥራ ሳይብረከረኩና መንግሥታዊ ግልበጣ ሳያቃዣቸው ሊኖሩ የሚችሉት በገለልተኛ መሠረት ላይ ዴሞክራሲ ሊገነባ ከቻለ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህን እውነቶች እኔ ነኝ ያለ የፕሮፓጋንዳ ሞራ ሊሸፍናቸው አይችልም፡፡ እነሱን አንድ ሁለት እያልኩ መደርደሬም ኢሕአዴግ አላወቀ ይሆናል የሚል የዋህነት ይዞኝ አይደለም፡፡ የአገራችን እውነታ ብዙ እርማትን የሚሻ መሆኑ ዓይን የማንቆር ያህል የሚታይ ነው፡፡ ማየት የፈለገም ማድረግ ያለበት ዓይኖቹን መክፈት ነው፡፡ ዓይን ከድኖ ሃራምባና ቆቦ የረገጠ መከራከሪያ ማቅረብ ትርፉ ዓይነ ደረቅነትን ማጋለጥ ብቻ ነው፡፡
ብሔርተኛ ገዥነት ከተቋቋመ ወዲህ በአገራችን የተፈለፈሉት ጣጣዎች ብዙ ናቸው፡፡ ማናለብኝ ያሉ ዝርፊያዎች፣ አድሎዎች፣ ንቁሪያዎች፣ የኃይል ጥቃቶች፣ መብት ጭፍለቃዎች፣ ፖለቲካዊ ሾኬዎች፣ ‹‹የቤቴ መቃጠል ለትኋን በጀኝ›› የሚሉ መሳይ ብልጠቶች፣ አላታሚ አሉባልታዎች፣ ወዘተ፣ ወዘተ፡፡ እነዚህን የመሳሰሉ መጠቃቂያዎች መርዛቸውና ሕመማቸው ቶሎ አይነቀልም፡፡ እኔ ነኝ ያለ አርቆ አሳቢ ሰውም ቢሆን፣ በብሔረሰብ ማንነቱ መገለልና መንጓለል ሲያርፍበት ወይም ለገዥ ፖለቲካ ባለማዘጥዘጡ ከተገቢ ጥቅሙና መብቱ ሲገፋ በጥቃት መመዝመዙ፣ ሚዛናዊና የእኩልነት አመለካከቱ እየተመረዘ ወደ ጅምላ ስሜቶች በመውረድና ባለመውረድ መሀል ቁም ስቅል ማየቱ አይቀርም፡፡ መጠራጠር፣ ድፍርስ ስሜቶችና ፍረጃዎች ከመቃቃር ጋር በአገራችን ፈጥነው የተባዙት ለዚህ ነው፡፡
የችግሮችን መነሻዎች በማስወገድ ረገድ ትርጉም የሚሰጥ ሥራ በማከናወን ፈንታ እንዲህ እንዲያ ያለው ድርጊት የትምክህተኞች/የጠባቦች ነው እያሉ ዛሬም ነገም ውግዘት መደርደር ህሊናን ከማታከትና ንቁሪያን ከማገልገል በቀር ትርፍ የለውም፡፡ ይህንኑ ትምህርት ለመስጠት የማያንስ ልምድም አሳልፈናል፡፡ የቅድመ ኢሕአዴጉ የሥልጣን ዘመን አማራ ገዥዎች የደመቁበትና አማርኛ ብቻውን የመንግሥታዊ ሥራ ቋንቋነቱን የተቆጣጠረበት መሆኑ በራሱ የሚረጨው መልዕክት ሳያንስ፣ ወደ ሥልጣን የመጡና የፖለቲካ ሜዳውን ያጣበቡ ብሔርተኛ ፖለቲከኞች ከዋናው የፖለቲካ ጥያቄ (ከፈላጭ ቆራጭነት ወደ ዴሞክራሲ የማለፍ ጥያቄ) ይልቅ የብሔር ጉዳይን ወደፊት በማምጣትና ነጋ ጠባ ስለትምክህት/ነፍጠኛ ኃይሎች በማባዘት አወቁትም አላወቁትም ጭፍን ጥቃት በአማራነት ላይ እንዲነሳ አግዘዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ የዴሞክራሲ ጥያቄ ተጭበርብሮ እንዲዘነጋ የማድረግ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ ከዚያም ወዲህ ሌሎች በስሜት የተግለበለቡ ቅስቀሳዎች የብሔረሰብ ግጭቶችን ሲያደርሱ ታይቷል፡፡ ከእነዚህ ልምዶች በመነሳት ብሔረሰባዊ ጥላቻዎችና የበቀል ስሜቶች እንዳይራገቡና እንዳይባባሱ መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡ ጥንቃቄያችን ግን ላይ ላዩን የሚሄድ፣ በስሜታዊነት የተሞሉ ቃላትንም ሆነ ለበቀል የሚያነሳሱ የጥቃት ዜናዎችን ባለመርጨት የግልፍታን አፍላ ሰዓት አሳልፎ፣ የድስኮራ ኮንፈረንስ ከማካሄድ በቀር ለመሸካከርና ለጥላቻ መፍለቂያ የሆኑ ዕውናዊ ችግሮችን የማስተካከል ሥራ ላይ አላተኮረምና ችግሩ ማብቂያ ሊያገኝ አልቻለም፡፡ በተለያዩ ክልሎች ስለተፈጸሙ ቤት ንብረት የማሳጣትና ሕይወት የመቅጠፍ ጥቃቶች አፍረጥርጠን እንተርክ ቢባል ቀላል የማይባል ጉድ አለ፡፡ የበቀል እሳት ላለማራገብ ሲባል የማለባበሳችንን ያህል ደግሞ የአማራ ትምክህተኞች ይህንን አደረጉ ለማለት አንደበታችንን አይዘንም፡፡ ከሌላ ብሔረሰብ ግድም ያገጠጠ የንቀትና የእብሪት ሥራ ሲያጋጥመን እንኳ ከትምክህት ጋር ለማገናዘብ አንደፍርም፡፡ ይህ ከምን የመጣ? ካለማወቅ? ወይስ ‹‹…የተሻረን ይመሰክሩበታል›› እንዲሉ ዓይነት ሆኖ?
ትምክህት ማን ያህለኛል ባይነት ነው፡፡ ዛሬ ካሉና ካለፉ፣ እውነተኛና ታሪካዊ ወይም አፈ ታሪካዊ ከሆኑ አኩሪ የተባሉ ክንዋኔዎችና ብልጫዎች ላይ ተጣብቆ፣ ከገዥነት ዝናዎችም ጋር የሚያዛምዱ ማኅበራዊ ክሮችን አፈላልጎ (ብጥስጣሾችንም ቢሆን ቆጣጥሮ) በመመፃደቅ የሌሎችን አስተዋጽኦዎች ማስተዋል የሚሳነው ነው ትምክህት፡፡ በዚህም ሚዛን በሳተ እሳቤውና ቁንንነቱ የሚገፋተር ንቀትን እየረጨ ማኅበራዊ መስተጋብሮችን ይቦረቡራል፡፡
ለዚህ ዓይነት ተመኪነት መነሻ የሚሆኑ ስንቆች አነሰም በዛ በበርካታ ማኅበረሰባዊና አካባቢያዊ አብራኮቻችን ውስጥ ማግኘት አይገድም፡፡ ለመመኪያነት ሊውሉ የሚችሉት ነገሮች ዝርዝራቸው ብዙ ነው፡፡ ለምለምና ሰፊ መሬት፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ፀጋ፣ የከበሩና የውድ ማዕድናት ፀጋ፣ የከተማ ሥልጣኔ መነሻ መሆን፣ የቀደምት ሥልጣኔ ባለቤት መሆን፣ ከሌላው ቀድሞ ክርስትናን/እስልምናን መቀበል፣ የአንዱ ወይ የሌላው ሃይማኖት ነባር ማዕከል መሆን፣ እምነትን፣ ባህልንና ቋንቋን በጥራት ጠብቆ የማቆየት ታሪክ አለኝ ባይነት፣ የአፍሪካዊ ዴሞክራሲና የአንድ አምላክ እምነት ቀዳሚ መገኛነት፣ የፍልፍል ሥነ ሕንፃ ባለታሪክነት፣ የሰው ዘር መገኛነትና የጥንታዊ ፊደል ባለቤትነት፣ ወራሪን በቆራጥነት የመታገል ታሪክ፣ የቅኝ ኃይልን ድል አድርጎ የመመለስና ቅኝ ያለመገዛት ታሪክ፣ ወርቃማ የኪነ ጥበብና የድርሰት ሰዎች ካፈራ አካባቢ መብቀል፣ አሮጌ አገዛዝን የታገሉ ብዙ ተራማጆች ካፈራ አካባቢ መብቀል፣ የትጥቅ ትግል ባለታሪክነት፣ ወዘተ፣ ወዘተ፡፡ ለአብነት ከቀረቡት ዝርዝሮች ውስጥ ሐረሪው፣ ከፋው፣ ወላይታው፣ ኦሮሞው፣ ትግሬው፣ ወዘተ መኩሪያዬ የሚሏቸው ነገሮች እንደሚኖሯቸው በአክሱምነት፣ በወለጌነት፣ በጎንደሬነት፣ ወዘተም ሊመነዘሩ የሚችሉ መኩራሪያዎች እንዳሉ፣ ከዚያም በላይ ለአገር ልጅነት የኩራት ሀብት ተደርገው

No comments:

Post a Comment