Wednesday, September 27, 2017

ሦስት ሺህ የሚሆኑ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ከሶማሌ ላንድ ተፈናቀሉ


Filed under: News Feature,የዕለቱ ዜናዎች |


 



(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል የድንበር ግጭት የተነሳ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከሁለቱም ክልሎች መፈናቀላቸው ሲዘገብ የቆየ ሲሆን  አሁን ደግሞ  ከጎረቤት ሶማሌላንድ ሦስት ሺሕ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች መፈናቀላቸው ተሰማ፡፡
እንደ ሪፖርተር ዘገባ ከሆነ የሁለቱ ብሔሮች ተወላጆች ግጭት ድንበር ዘሎ ኢትዮጵያ ከሕግ በመለስ እንደ አገር ዕውቅና በሰጠቻት ሶማሌላንድ ውስጥ የሚኖሩ ከሦስት ሺሕ በላይ ኦሮሞዎችም መባረራቸውን፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

የተፈናቀሉት የኦሮሞ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን በአሁኑ ወቅት ቶጎ ውጫሌ በሚባለው የኢትዮጵያ ድንበር እንደሚገኙና ወደ ኦሮሚያ ክልል በመግባት ላይ መሆናቸውን ዶ/ር ነገሪ ገልጸዋል::

No comments:

Post a Comment