አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ፣ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ እና የኢትዮጵያ ጥንታዊ አርበኞች ሊቀ መንበር ለአስታራቂነት ተጠርተዋል።የክፍፍሉ አሰላለፍ ተለይቷል።

በሌላ በኩል የክፍፍሉ መነሻ በአስተዳደር ጉዳይ ላይ ብቻ ሳይሆን ከሀገሪቱ በተዘረፈ ጉዳይ ዙርያ የሁሉም እጅ ከመኖሩ አንፃር አንዱ ከአንዱ የተሻለ መሆኑን ለማሳየት የሚደረግ ጥረት እና በእዚሁም ሳብያ አንድኛው ቡድን ሌላውን ለማሰር ከማሰብ የተነሳ እንደሚሆን ሲነገር ሰንብቷል።
ኢሳት በራድዮ ፕሮግራሙ ላይ እንደገለፀው ክፍፍሉን ተከትሎ በሕወሓት በእራሱ በተመረጡ የገለልተኛ ቡድን ደረግ የነበረው ሽምግልና ፍሬ ባለማስገኘቱ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ፣ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ፣ የኢትዮጵያ ጥናታዊ አርበኞች ሊቀ መንበር ልጅ ዳንኤል ጁቴ እና ነጋዴዎችን ያካተተ መሆኑ ተሰምቷል።
የክፍፍሉ አሰላለፍ
1ኛ/ በጀነራል ሳሞራ የኑስ የሚመራው ስር የሚገኙ : –
– በወታደራዊ መረጃ ኃላፊ ሜጀር ጀነራል ገብሬ ዲላ ፣
– የሜቴከ (ብረታብረት ኢንጂነሪንግ) ኃላፊ,
– የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አባይ ወልዱ እና
– የአቶ መለስ ባለበት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ሲገኙበት
2ኛ/ በአቦይ ስብሐት የሚመራው ቡድን ስር የሚገኙ : –
– አቶ አባይ ፀሐዬ እና
– የደህንነት ኃላፊው አቶ ጌታቸው አሰፋ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።
3ኛ/ ዶ/ር ደብረ ፅዮን እና ዶ/ር አርከበ እስካሁን ከየትኛው ቡድን እንደተሰለፉ አልታወቅም።
የኢትዮጵያ አምላክ ይፈርዳል ሳይውል ሳያድር
በድምፃዊ ኃይልዬ ታደሰ
No comments:
Post a Comment