Wednesday, April 26, 2017

ኃይሌ ገ/ስላሴ ከመጋረጃው ጀርባ የሚሰራውን ምን ያህል ያውቃሉ?

   


ኃይሌ ገ/ስላሴ ከመጋረጃው ጀርባ!!
ኃይሌን በአደባባይ የምናውቀው በእግሮቹ ፍጥነት ነው፡፡ ከአደባባይ በመለስ ከመጋረጃው ጀርባ የሚሰራውን ምን ያህል ያውቃሉ?
ኃይሌ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ጤፍ (The Ethiopian endemic crop) ከወንድሙ ጋር በመሆን እና ከሆላንድ ባለሀብቶች ጋር በመመሳጠር ባለቤትነቱ በሆላንዳዊያን አንዲ መዘገብ አድርጓል፡፡ሀይሌ እና ወንድሙ ከሆላንድ ባለሀብቶች ጋር በፈጠሩት ሽርክና ጤፍን ከኢትዮጵያ ውጭ በማምረት እና በማሰራጨት ሀገሪቱ በዚህ ብርቅየ አዝዕርት ማግኘት የነበረባትን ጥቅም አሳጥቷታል፡፡
ኃይሌ በወቅቱ ስለዚህ ጉዳይ የወያኔውን ሪፖርተር ጋዜጣን ጨምሮ የተለያዩ ሚዲያዎች ጥያቄን ቢያቀርቡለትም መልስ ለመስጠት ፍቃደኛ አልነበረም፡፡ “የኢትዮጵያ የዘረመልህ ባንክ” የሚባለው ተቋም የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች የኃይሌን ተግባር ቢቃወሙም፤ የህወሓት የዘረፋ ሸሪክ በመሆኑ ምንም የተባለው የለም፡፡ እንዲያውም ይህ ጉዳይ በVOA ቀርቧል፡፡
የኢትዮጵያ አንጡራ የተፈጥሮ ፀጋን የዘረፈው እና ያዘረፈው ኃይሌ፤ እንደ መደኃኔት በአለም አቀፍ ደረጃ ከሚሸጠው ጤፍ ላይ ሀብት እያካበተ ነው፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ አንድ ሀገር በብቸኝነት ላላት የተፈጥሮ ፀጋ ልዩ መብት የሚሰጥ የባለቤትነት መብት አለ፡፡ ኃይሌ ኢትዮጵያ ያሳጣት ይህንን ልዩ መብት ነው፡፡ የማምረት እና የመሸጥ ፍቃድ በመስጠት ብቻ ኢትዮጵያ በአመት ሚሊዮን ዶላርሮችን ማግኘት የምትችልበትን መብት ነው ያሳጣት፡፡
ሌላኛው የኃይሌ እና የወያኔ የንግድ ሽርክና “ማራቶን ሞተርስ” ነው፡፡ ይህ የኮሪያን ቅንጡ ተሽከርካሪዎችን የሚያስመጣው ተቋም ዋንኛ ሸማቾች የወያኔ መከላከያ ሚንስቴር መስሪያ ቤት ነው፡፡ ሌሎችም የወያኔ የመንግስታዊ ተቋማት ሸማቾች ናቸው፡፡ኃይሌ በአንድ ወቅት የመኪና ንግድ በወራት በመቶ ሚሊዮኖች የሚታፈስበት ነው ብሏል ለሪፖርተር ጋዜጣ፡፡ በመቶ ሚሊዮኖች የሚታፈሰው ለኢትዮጵያ ህዝብ ሸጦ ሳይሆን ለመንግስታዊ ተቋማት በተመቻቸለት የልዩ ተጠቃሚነት መብት ነው፡፡ በኢትዮጵያ አንደኛ የመኪና ሻማቾች የመንግስት ተቋም ተብየዎች መሆናቸው ግልፅ ነው፡፡
ኃይሌ ከሩጫ የተሸለመው ጥቂት ምሊዮኖች ነው፡፡ ከስፖንሰር የሚያገኘውም ቢሆን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ምክነያቱም ስፖንሰር የሚያደርጉት አለማከፍ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያጓጓ የገብያ ድርሻም የላቸውም፤ ምርታቸውም ለአብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች የሚቀመስ ዋጋ አይደለም፡፡ የኃይሌ ሀብት ግን በቢሊዮኖች የኢትዮጵያ ብር ነው፡፡
ስለዚህ የኃይሌ የሀብት ምንጭ ከወያኔዎች ጋር የሚደረግ የዝርፊያ ሽርክና ነው፡፡
ሌላው የሀይሌ ገራሚ ነገር ለአፍሪካውያን በተለይም ለኢትዮጵያውያን ያለው የተዛባ አመለካከት ነው፡፡ ይህንንም በBBC ላይ ለአፍሪካውያን ዲሞክራሲ አያስፈልግም ብሏል፡፡ ምክነያት እሱ ከጨቋኞች እና ከዘራፊዎች ጋር መሞዳሞድ ስለሚችል ነው፡፡

No comments:

Post a Comment