Monday, April 3, 2017

ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ላለፉት 20 አመታት ለበረከተው አሰተዋአዖኦ ለታላቅ ሽልማት እና እውቅና በቃ !!!

    


ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ላለፉት ☞ 20 አመታት ለበረከተው አሰተዋአዖኦ ለታላቅ ሽልማት እና እውቅና በቃ !!!
FB_IMG_1491228273669

የ25ኛው የማኅበረ ግሩያን ዘረ ኢትዮጵያ ልዩ የእውቅ እና የአክብሮት ሽልማት ይካሄዳል ! መርሐ ግብር ቅዳሜ ሜይ 28 ቀን 2017 በአሜሪካን አገር ይካሄዳል።

በሚያካሂደው የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ” ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ” በሚል መርህ ዘንድሮ ለ25ኛ ጊዜ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ይካሄደል።

ዘንድሮ 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በአሉን የሚያከብረው ማኀበረ ፣የዘር ግንዳቸው ከኢትዮጵያ የሚመዘዝና እንዲሁም በትውልድ የሌላ አገር ተወላጅ ሆነው ፤ለኢትዮጵያ መልካም ነገርን በተለያዩ የሙያ ዘርፍ ያበረከቱትን በየአመቱ በሚያካሂደው
የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ፣ ክብር ለሚገባው ክብር ይሰጣል።

ዘንድሮ ማኀበረ የምስረታውን 25 ኛ አመት የብር ኢዮቤልዩ በልዩና በደመቀ ሁኔታ ለማክበር በተዘጋጀበት ወቅት፣ የ25ኛው አመት ልዩ የክብርና የእውቅና መርሐግብር ተሸላሚዎች መካከል #ልዩ_ተሸላሚ አድርጎ የመረጠው (y) ድምጻዊ #ቴዎድሮስ_ካሳሁን_ገርማሞን ነው !!!

✍ ቴዲን ልዮ ተሸላሚ የሚያደርገው በሥነ ፅሁፍ ዘርፍ ታላቅ የግጥም ፀሐፊ፣ በሙዚቃው ዘርፍ ታላቅ ድምፃዊና የዜማ ደራሲ፣ በታሪክ ዘርፍ ስለ ኢትዮጵያ ምድሯና ህዝቦቿ፣ባህሏና ትውፊቷ፣ ጀግኖቿና አንፀባራቂው ድሏ፣ የሃይማኖት መቻቻልና የታላላቅ ልጆቿን ገድል በሥራዎቹ በማሳየቱና ለትውልዱ ልዩ የታሪክ ተናጋሪ በመሆኑ እና የበርካታ የሙያና የሰብአዊ አገልግሎቶች ባለቤት በመሆኑም ጭምር ነው።

✍ ቴዲ አፍሮ ለሕዝብ ባቀረባቸው አራት የሙዚቃ አልበሞቹና በርካታ ነጠላ ዜማዎቹ እስካሁን በኢትዮጵያ ምድር ድምፃዊነትን ከግጥምና ዜማ ደራሲነት ጋር አዳምሮ በብዛትም፣ በጥራትም በሕዝብ ተቀባይነት በማገኘትም እንዲሁም በሽያጭም ተወዳዳሪ ያልተገኘት የሙያ ባለቤት ነው ።

♦በሼመንደፈር ☞ የሐይማኖት መቻቻልን ፣
♦በጥቁር ሰው ☞ አርበኝነትን፣
♦በያስተሰርያል ☞ እርቅን ፣
♦ በካብ ዳኀላክ ☞ የመለያየት ከባድነትን፣
♦በፀባዬ ሰናይ ☞ ትዳርን ፣
♦በአቡጊዳ ☞ ፊደል አስቆጣሪዎቻችንን ፣
♦በስለ ፍቅር ያሳለፍነው ዘመናችንን፣
♦በሰባ ደረጃ ☞ የጥንቷን ሸገርን፣
♦ በኡኡታዬ ☞ የዘመናት ጩኸታችንን ፣
♦በታሪክ ተሰራ እና ☞ ኃይሌ ኃይሌ የኦሎምፒክ ውሏችንን፣
♦በግርማዊነትዎ ☞ አፄ ኃይለ ሥላሴንና ፓን አፍሪካን፣
♦በዋልያ ☞ ብሔራዊ ቡድናችንን፣
♦ በኮርኩማ አፍሪካ ☞ ስደታችንን እና ስለ በርካታ የሰው ልጆች የሕይወት ውጣ ውረድን፣ ስኬትን፣ ሃዘንን፣ ደስታን ወዘተርፈ የሚዳስሱ ስራዎቹን ላለፉት ☞ 20 አመታት ለአድማጭው አድርሶ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትን አገኝቷል።

ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ ! ፍቅር ያሸንፋል !!!

የዚህ የዜና ምንጭ እና መረጃ © ጴጥሮስ አሸናፊ ነው። እኔም (ይድነቃቸው ከበደ) በእንዲህ መልኩ መረጃው እንዲዳረስ አድርጌያለሁ። ለቴዲ ካለኝ ክብርና አድናቆት ብቻ !

No comments:

Post a Comment