Sunday, April 2, 2017

በወልድያ ከተማ የትግራይ ተወላጆች መንግሥት ትጥቅ እንዲፈቅድላቸው ጠየቁ – (ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋው )



By ሳተናውApril 2, 2017 10:45






 1  81  82
ከባለፈው ሐምሌ ወር የዐማራ ተጋድሎ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በወልድያ ከተማ አዳጎ እና ፒያሳ የሚባሉ የንግድ ተቆጣጥረው የሚገኙ የሕወሓት አባላት የትግራይ ተወላጆች መንግሥታቸው የተለየ ጥበቃ እንዲያደርግ ጠይቀው የፀጥታ አካላት ተመድበው ሲጠብቁ ቆይተዋል፡፡
ሆኖም ባለፈው ሳምንት ለሰሜን ወሎ ዞንና ለወልድያ ከተማ አስተዳደር የንግድ ተቋማችንና ራሳችን ለመጠበቅ መንግሥት ትጥቅ ሊያስታጥቀን ይገባል በማለት የትግራይ ተወላጆች በሕብረት ጥያቄ እንዳቀረቡ ሰምተናል፡፡ በወልድያ ከተማ አብዛኛዎቹ የንግድ ተቋማት በትግራይ ተወላጆች ቁጥጥር ሥር ሲሆኑ የአካባቢው ተወላጆች በልዩ ልዩ ሰበብ ከንግድ እንዲወጡ አሊያም አካባቢውን ለቀው እንዲሔዱ ይገደዳሉ ተብሏል፡፡
በከተማው የንግድ እንቅስቃሴ ማዕከል የሆኑት ከአዳጎ እስከ ፒያሳ ድረስ ሁሉም በአንድ ብሔር ተወላጆች የተያዘ እንደሆነ ነው ነዋሪዎች የሚገልጹት፡፡

No comments:

Post a Comment