Saturday, April 22, 2017

የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ሕጎች ረቂቆችን እያወጣ ነው

የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ሕጎች ረቂቆችን እያወጣ ነው

በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት ኢትዮጵያን በተመለከተ የሚቀርቡ የውሣኔ ሀሳቦችን «በተሳካ ሁኔታ አምክኛለሁ» ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ቢናገርም ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ህጎች አሁንም በኮንግረሱ እየረቀቁ መሆናቸውን የህዝብ ተወካዮች አመልክተዋል።
በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት ኢትዮጵያን በተመለከተ የሚቀርቡ የውሣኔ ሀሳቦችን «በተሳካ ሁኔታ አምክኛለሁ» ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ቢናገርም ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ህጎች አሁንም በኮንግረሱ እየረቀቁ መሆናቸውን የህዝብ ተወካዮች አመልክተዋል።
የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ በመጋቢት መጨረሻ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሁለት ረቂቅ ህጎችን እንዳጨናገፈ የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የኮንግረሱ የአፍሪካ ንዑስ ኮሚቴ ሊቀመንበር ለዝግጅት ክፍላችን በሰጡት ማብራሪያ «ኮንግረስ በምርጫ ሲቀየር ህጎች እንዳዲስ ለውሳኔ ይቀርባሉ እንጂ የተጨናገፈም ሆነ እንዲዘገይ የተደረገ ህግ የለም» ብለዋል።

No comments:

Post a Comment