Monday, June 5, 2017

በጎንደር ቅዳሜ ሌሊት የተኩስ ልውውጥ ነበር | የኢትዮጵያ ህዝብ ለወሳኙ ትግል ጥሪ ቀርቦለታል



File Photo
ከሙሉነህ ዮሐንስ
በሰሜን ጎንደር በሁለት ግንባር የጎበዝ አለቆች ላይ የከፈተው የማጥቃት እርምጃ የከሸፈበት ወያኔ ብዛት ያለው ተጨማሪ ጦር ወደ አካባቢው እየላከ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ቅዳሜ ሌሊትም አንድ ግንባር ላይ የጋለ የተኩስ ልውውጥ ነበር። በወገን ላይ የደረሰ ጉዳት የለም። የወያኔ ወታደር ግን እየደነበሩ ወደ ገደል መግባታቸው ታውቋል።
ስለሆነም ህዝቡ ይህን ወያኔ የከፈተበትን የእብሪት ጦርነት አውቆ የጥንቃቄ እርምጃ እንዲወስድ ከግንባር መልእክት ተላልፏል። ሰሞኑን ተቋርጦ የነበረው ኢንተርኔት በመጠኑ ተለቋል።
ወያኔ ጎንደር ላይ ብዛት ያለው ወታደር እያከማቸ መገኘቱ በህዝባችን ላይ ጅምላ ፍጅት እስከማድረግ ስለማይመለስ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ። ለኢትዮጵያ ህዝብ ድምፅ የሆነው አመት ሙሉ ከባድ ተጋድሎ እያደረገ ለሚገኘው የጎንደር ህዝብ ከሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ አስቸኳይ ድጋፍ መደረግ አለበት።

No comments:

Post a Comment