Friday, June 23, 2017

የ34 ኢትዮጵያውያን ጉዳይ በኬንያ – ጥላየ ታረቀኝ


By ሳተናውJune 23, 2017 03:17



የ34 ኢትዮጵያውያን ጉዳይ በኬንያ – በሀገራችን ኢትዮጵያ ህገ-ወጥ የሰዋች ዝውውር ከፍተኛ የሆነ ጉዳት እያመጣና እያደረሰ መሆኑን ንፁሀንንና በእድሜ ያልጠነከሩ ለጋ ወጣቶችን እያረገፈ መሆኑን ለኢትዮጵያንና በዚህ ማህበራዊ ድህረ ገፅ ላይ ላላችሁ ወገኖቼ መንገር ለቀባሪ ማርዳት ይሆንብኛል ለምሳሌ በሊቢያ በግብፅ ሲና በርሃ በሜዲትራኒያ ባህር እንደጉድ የሚረግፉ ወገኖቻችን ቁጥር ቤት ይቁጠረው ይሄ ህገወጥ የሰዋች ዝውውር ጉዳዩ ያላንኳኳው ቤት የለምና ሁሉንም አንገት ያስደፋ ጉዳይ ነው።
ከኢትዮጵያ ደቡብ ክልል በዚህ ባሳለፍነው ሳምንት 34 ኢትዮጵያውያን በሞያሌ በኩል በማድረግ በህገወጥ የሰዋች አዝዋዋሪ ወይም ሰው በቁሙ በሚሸጡ የሰው ነጋዴዋች አማካኝነን ኬንያ ይገባሉነገሩን ከመነሻው ከሀገራቸው ኬንያ መግቢያ ቦርደር ጀምሮ ሲከታተል የነበረው የኬንያ ፓሊስ እነዚህን ወጣቶች ከናይሮቢ ወጣ ብሎ tika towen ተብላ በምትጠራ ትንሽ ከተማ ውስጥ በህገወጥ የሰዋች ዝውውር ላይ ተሳታፊ በሆኑ ሰው ሻጭ የእፍኚት ልጆች አማካይነት በተከራዬት ቤት ውስጥ እነዚህን ወጣቶችና በእድሜ አነስተኛ የሆኑ ለጋ ታዳጊዋች በአንድ ክፍል በማጎር ለተወሰነ ቀን ከዚህ ቀደም እንደሚያረጉት እንደልማዳቸው ወጣቶችን አፍነው በማቆየት ወደ ደቡብ አፊሪካ ለመላክ የተያዘው እቅድ ግን አልተሳካም
በአካባቢው ሰዋች ጥቆማና በኬንያ ፓሊሶች ክትትል እነዚህ ምንም የማያውቁ ነገ የተሻለ ኑሮ ትኖራላችሁ በሚል ስብከትና አጉል ተስፋ ተታለው ከፍተኛ ክፍያ በመክፈል ወደ ደቡብ አፊሪካ ለመሄድ የታቀደው እቅድ ሳይሳካ በኬንያ ፓሊስ እጅ ይወድቃሉ ሁኔታው በጥሞና ሲከታተል የነበረው የኬንያ ፓሊስ እነዚህ 34 ኢትዮጵያ በመያዝ እዛው ትንሽ ከተማ ውስጥ በሚገኘው juja police divisonal head quarters በሚባል ፓሊስ ጣቢያ ውስጥ ያስራቸዋል በተያዙ በማግስቱ እዛው ትንሽ ከተማ ፍርድ ቤት በመቀርብ ሰው ሀገር ላይ በህገወጥ መልኩ በመግባታቸውና ማንነታቸውን የሚገልፅ ምንም አይነት ማስረጃ ወረቀት እጃቸው ላይ አለመኖሩን ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን በማጣራት 27 ላይ የአራት ወር እስርና እስራቸውን ሲጨርሱ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱና ይወስናል ቀሪዋቹ ሰባት ወጣቶች እድሚያቸው ለፍርድ ያልደረሰ በመሆኑ በአስቸኮይ ወደ ኢትዮጵያ ይመለሱ የሚል ፍርድ በመፍረድ ፍርድ ቤቱ አማካኝነት ውሳኔው ይተላለፋል
ይሄ ፍርድ ቤት እነዚህ ኢትዮጵያውያን በቀረቡ በአንደኛው ቀን 27ቱ ወደ ከርቸሌ እንዲጎዙ ሲያረግ ሰባቱ ደግሞ እዛው ፓሊስ ጣቢያ ቆይተው ወደ ኢትዮጵያ ዲፖርት ወይም ይመለሱ ዘንድ ወስኖል ። እኔ ግን ወጣቶችን በዛች ጠባብ ክፍል በአካል አግኝቼ ሳዋራቸው በህገ-ወጥ ደላሎች ተታለው ከሀገራቸው ደቡብ ክልል ተነስተው ወደ ደቡብ አፊሪካ ለመሄድ ማሰባቸውንና አሁን ግን ሁሉም ነገር እንደጨለመባቸው ሲያጫውቱኝ እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ አይዞቹህ ከማለት ውጪና በእጄ የያዝኮትን ከወገን በመጠየቅ የእለት ውሃና ምግባቸውን በመግዛት ከዚህ ውጪ ሌላ ማድረግ እንደማልችል በማስረዳት ተሰነባብቼ መውጣቴን እናም በሁለተኛ ቀን አሻራ ሰጥተው ወደ ሀገራቸው ሊገቡ መሆናቸውን ሲነግሩኝ እጅግ ደስታዬ ብዙ ሆኖ ተመለስኩኝ የሚገርመው ግን እኔ ለማጣራት አስቤ እዛው ከተጠቂዋቹ ጋር በአካል ተገኝቼ የጠየኮቸው ጥያቄዋች አለ ወጣቶች ማን ሊረዳችሁ መጥቶ ነበር ብዬ ነበር በመጀመሪያ የወጣቶችም መልስ ማንም መጥቶ ጠይቆን አያውቅም ነው !!! #
የዋህ_ነህ_ወይ_አትበሉኝና ~~~ በዚህ ናይሮቢ ኬንያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤንባሲ ተብየው በዚሁ ናይሮቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ተብሎ EBS ላይ ኬክ ሲቆርሱ የነበሩ ግለሰቦች ወይም ልክ እንደ ዜጋ በናይሮቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሀይማኖት መድሀኔአለም ቤተክርስቲያን እንዲህ ስደተኛ ወገን ዜጎች ሲንገላቱ የሰው ልጅ እንደከብት ሲሸጥ ሌሎችም የሀይማኖት ተቆማት ድምፅ ሳያሰሙ ዝም ማለት ወይም ዝምታው እስከመቼ ነው ወገን እያለቀ: በተረፈ ግን @~~ ይህ ሁሉ ወገን ሲሰቃይ ሲንገላታ ሲጉላላ እንደሸቀጥ ሲሸጥ በቃ ልንል ይገባል ወገን በተቸገረና በተጨነቀ ሰአት ከጎን መቆም ካልቻለ ምኑን ነው ኢትዮጵያውያንን የሚወክለው ጠንከር አርጌ እነዚህ ኢትዮጵያውያንን እንወክላለን የሚሉ አካላትን መጠየቅ የምሻው እውን ይሄን ዜና አልሰሙ ይሆን ? ወይስ በዚህ የሰዋች ንግድ ላይ እጃቸው አለበት የሚለውን ጥያቄ ይመልሱልኝ ዘንድ ነው ? በዚህም የወገን ጉዳይ ላይ አይናቸውን ሳያሹ ዜናውን ሰምተው ድንገት ተርበው ይሆናል በማለት አቅማቸው የፈቀደውን ያደረጉ ትልቅ ምስጋና የሚገባቸው ሁለት ቅን ኢትዮጵያን habtamu tadege እና gelila legesse የተባሉ ድንቅ ኢትዮጵያውያን ለእነዚህ ወገኖች ምስጋና አቀርባለሁ ለአራት ቀን የሚሆን ምግባቸውንና ውሃ ገዝተው እንዲበሉ አድርገዋል ኢትዮጵያዊ ወገንተኝነታቸውን በተግባር አሳይተዋል እናም የኢትዮጵያ አምላክ ውለታችሁን ይመልሳላችሁ ከማለት ውጪ ሌላም የለኝ ። #ግን_እስከመቼ ??? #ኢትዮጵያ_ለዘላለም_በክብር_ትኑር

No comments:

Post a Comment