Saturday, June 3, 2017

በአዳማ ከተማ 80 የሚደረሱ የህዝብ ሱቆች በእሳት ቃጠሎ መውደማቸው ተዘገበ።

    



በአዳማ ከተማ 80 የሚደረሱ የህዝብ ሱቆች በእሳት ቃጠሎ መውደማቸው ተዘገበ።
በአዳማ ከተማ አውቶብስ መናሪያ አከባቢ በተለምዶ ፍራንኮ ገበያ በምባል በምጠራ ቦታ በተነሳ እሳት ቃጠሎ እሰከ 80 የምደረሱ ሱቆች በትላንትናው እለት እንደ ወደሙ ምንጮች ለራዳሃ ገለፁ።
ይህ የእሳት ቃጠሎ የደረሰው ትላንት ማታ ከ4 ሰዓት ጀምሮ አሰከ ጠዋት የቆየ ስሆን አስከ አሁን በደረሰን ዘገባ የእሳቱ መንስኤ ምን እንደሆነ ያልታወቀ ስሆን በመንግስት በኩል እሳቱን ለማጥፋት የተደረገ እገዛ እንደለለ እና እሳቱን የምያጠፋ ውሃ 30ኪሜ ከብሾፍቱ ከተማ በማምጣት እንደነበረ ገልፀውልናል።
ምንጮቻችን እንደገለፁ አንድ የኦሮሞ ባለ ሀብት ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የምገመት ንብረት የወደመበት ስሆን በአዳማ ከተማ የምኖሩ ህዝቦች እሳቱን ለመቆጣጠር እሰከ ንጋቱ ድረስ ከባድ ጥረት እያደረጉ እንደነበር ተገልፀዋል።
ይሄን ዘገባ የላከልን ምንጭ እንደምለው የምያሳዝነው ንገር ብኖር በእሳት ከወደመው ንብረት በላይ መኪና አቁመው ሱቁን በመሰበር ንብረትን በመኪና በመጫን የነበሩ ዘራፍዎች ናቸው ያሉትና የሰላም አስከባሪ ሀይል በቦታው አለመገኘት ህዝቡን የበለጠ እነደቆሰለ ምንጮቻችን ገልፀዋል።
የወደመው ንብረት ባለ ሃብቶቹ በህጋዊ መንገድ ግብር ለመንግስት እየከፈሉ እንደነበር ምንጮች ዘግበዋል።
ምንጮች እንደገለፁ የቃጠሎ አደጋ የደረሰው የሙስልም ሱቆች በብዛት ባሉበት ቦታ እንደሆነና ሙስልሞች ለተራዊህ ሰላት ሱቆቹን ዘግተው በነበረበት ወቅት መሆኑ ተዘግበዋል።
መንግስት የብሄራዊ ፈተና ሰበብ በማድረግ ኔትወረክ መዝጋቱ ይታወቃል።
በመንግስት በኩል እስከ አሁን ባገኘነው ዘገባ ምንም የተደረገ እንቅስቃሴ እንደሌለ ገልፀውልን ከእሳት ቃጠሎ በኌላ በሀገር ውስጥ ኔትወርክ መዝጋቱ ለምን እንዳስፈለገ እውነት ለብሄራዊ ፈተና ነው ? የምል ጥያቈን አጭሩዋል.
መንግስት ይህን እሳት ለማጥፋት ያደረገዉ እነቅስቃሴ የለም ማለት ይቻላል በተጨማሪም ዘራፍዎች መኪና በማቆም ዘረፋ ሲያካሄዱ ሰላም አሰከባሪዎች በአከባቢው ለምን አልተገኙም?የምሉ ጥያቄዎች በማህበረሰቡ ዘንድ ተነስተዋል በማለት ዘግበውልናል።

No comments:

Post a Comment