Tuesday, November 7, 2017

የአማራ ብሄር ተወላጆች ከአሶሳ ከተማ እንዲወጡ እየተደረገ ነው

(ኢሳት ዜና ጥቅምት 28 ቀን 2010 ዓም) ኤች አይቪ ቫይረስ አለባቸው የተባሉ የአማራ ብሄር ተወላጆች ከአሶሳ ከተማ እንዲወጡ እየተደረገ ነው
በቤንሻንጉል አሶሳ ከተማ የሚኖሩ ምግብ ና የጀበና ቡና በመሸጥ የሚተዳደሩ የአማራ ሴቶች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአስገዳጅ ሁኔታ የኤች አይቪ ምርመራ እንዲያደርጉ እየተገደዱ ሲሆን፣ ቫይረሱ ተገኝቶባችሁዋል የተባሉት ሴቶች ከስራ ቦታቸው ተፈናቅለው ወደ ክልላቸው እንዲሄዱ መገደዳቸውን ለአማራ ክልል ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እንዲሁም ለአማራ ክልል ሴቶችና ህፃናት ቢሮ ማመልከታቸውን ከቢሮው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። የሴቶችን አቤቱታ ተከትሎ ከክልሉ ቢሮ አጣሪ ኮሚቴ ተመድቦ ወደ አሶሳ መላኩን ለማወቅ ተችሎአል። ድርገቱ የክልሉን ተወላጆች ከቤንሻንጉል ክልል ለማስወጣት የተቀየሰ አዲስ ስልት መሆኑን ምንጮች ገልጸዋ...ል።
በሌላ በኩል ሰሞኑን በሳምንቱ መጨረሻ በፋሲል ከነማ እና ውልዋሎ አዲግራት መካከል የተካሄደውን ጨዋታ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት ደማቸው የፈሰሰውን ወጣቶች ደም ደም እንመልሳለን በማለት ሁከት ለመቀስቀስ እንቅስቃሴ ጀምረዋል የተባሉ ወጣቶች ተለይተው በክትትል ውስጥ እንዲገቡ እና የእጅ ስልካቸውም እንዲጠለፍ መደረጉን የፖሊስ ምንጮች ገልጸዋል።
ትናንት በነበረው የፖሊሶች ስብሰባ ላይ ኮማንደር ተኮላ " ደህና ወደ ሰላም የመጣውን ህዝብ እራሳቸው እየነካኩ ሌላ ችግር እየፈጠሩብን ነው፣ አሁን እንደገና የሞተ ሴል ነፍስ እየዘራ ነው፣ ካሁን በሁዋላ እነሱ እዛ እየነካኩ እዚህ ችግር ቢፈጠር እኛ ተጠያቂ አንሆንም” በማለት መናገሩን የፖሊስ ምንጮቻችን ገልጸዋል።


1 comment:

  1. Best casinos where you can play Slots and Win - ONE Casino
    The 암호화폐란 Slots and win slot machines offer the casino's 비트코인 시세 사이트 players a chance club w88 to win real money at a decent price in an effort to 1xbet korean win 토토 랜드 같은 and win. These slot machines

    ReplyDelete