Tuesday, November 7, 2017

ሰበር_መረጃ ደሴ ነጋዴዎች የስራ ማቆም አድማ ጀምረዋል፡፡



#ሰበር_መረጃ
#በዛሬው እለት በደሴ ከተማ ልዩ ቦታው አራዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የደሴ ከተማ ትልቁ የንግድ ማእከል በሆነው ቦታ አምስት ትልልቅ ህንፃዎች በድምሩ ከአንድ ሺህ በላይ ሱቆች የስራ ማቆም አድማ ጀምረዋል፡፡
************
#አገዛዙ በህዝብ ላይ ጥሎት የቆየው ካቅም በላይ የሆነ የግብር ክፍያን በመቃወም በአካባው ይነግዱ የነበሩ ባለሱቆች ሱቆቻቸውን መዝጋታቸውና ስራ ማቆመማቸው ታውቋል፡፡ ነጋዴዎቹ እንደሚሉትም አገዛዙ ያለ ሃቅማችን መክፍል የማንችለውን ግብር ጥሎብናል የተጣለብን ግብር ከጠቅላላው ገቢያችን የበለጠነው በማለት ቅሬታቸውንም አሰምተዋል የአገዛዙ አገልጋይ የሆኑ የቀበሌው ሹሞችም በቦታው በመሆን ሱቃችሁን ካልከፈታችሁ እርምጃ እንወስዳለን እያሉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ነጋዴዎቹም በበኩላቸው የዚህ ስርዓት አምባገነንነትና ዘራፊነቱን ተገንዝባችሁ ሌሎቻችሁም የአካባቢው ሰዎች የነዚህን ነጋዴዎች ፈለግ በመከተል አገዛዙን እምቢ አልገዛም ያለ አግባብ ግብር አልከፍልም ለሹሞች መበልፀጊያ ይሆን ዘንድ የልጆቼን ጉሮሮ አልዘጋም በማለት የዚህ ትግል አካል እንድትሆኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ውድ ተከታታዮቻችን ከስፍራው የሚደርሱንን መረጃዎች እየተከታተልን የምናቀርብ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ
አስተያየትዎን ይፃፉ

No comments:

Post a Comment