Thursday, August 31, 2017

ወያኔ እጁ ራጅም ነው በ ደቡብ ኮርያ በስደተኞች የተመሰረተውን መሐበረ ማሪያም አፍሪሶ በራሱ የበግ ለሚድ በለበሱ ሰዎች ልተካ ከጫፍ ለይ ደርሱዋል።


     |



“ሰውን ብትታገልና ብትዋጋ ታሸንፈዋለህ፤ወይም ያሸንፍሃል፤ ቤተክርስቲያንን ግን ማሸነፍ አይቻልም፡፡ ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ ትዋጋለች፤ተሸንፋም አታውቅም፡፡ዲያብሎስ ዝናሩን አራገፈ ቀስቱን ጨረሰ ቤተክርስቲያንን ግን አልጎዳትም፡፡” ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
መሐበረ ማሪያም በ ደቡብ ኮርያ በስደተኞች ስመሰረት እጅግ በጣም ልብ በሚነካ አሳዛኝ ሁኔታ ነበር። መሐበሩን ከመሰረቱት ፩፪ ሰዎች አንዱዋ አህቸታው በስደት ባረፈችበት ወቅት ፈጣሪያቸው በስደት ሃገር አንዲያስባቸው አንዲያበረታቸው በመከራና በወጀብ ጊዜ ፈጣርይ ብሪታቱና ጉልበቱን አንዲሰጣቸው ስሙንም ለማሰብ በየቤታቸው በጸበል እና ጻዲቅ መልክ የጀመሩት መሃበር አድጎ ዛሬ ደቡብ ኮሪያ ዉሲጥ ለሚኖሩት ክርስቲያኖች መሰባሰብያቸው ሊሆን በቅቱዋል። መሃበሩ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ እስክ ቅርብ ጊዜ ድረስ እጅግ በሚያስቀና እና በሚያስደምም ሁነታ በርካታ ተግባራትን ሲያከናዉን ቆይቱዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የአይናችሁ ቀለም አላማረኝም የሚለው ወያኔ ለትምህርት ወደ ደቡብ ኮሪያ በምልካቸው አባላቱ በኩል መሃበሩ ግራ የተጋባና ያልተግባባ በማድረግ በራሱ ሰሪጎ ገቦች በኩል የመሃበሩን አካሄድ ጠምዝዞ ወደሚፈልግበት አቅጣጫ ለመምራት ኢንድሁም ሰው እንቅልፉን አቶ አካሉን አጉድለው መከራዉን እየበላ ለቤተክርሲቲያን ማሰርያና ሙዳዬ ሚጹዋት የሚሰጠዉን ገንዘብ ለመቀራመት ወኪሎቹን አስከ መሃበሩ አመራር በማስረግ ከቻለ ከኢምባስው ቀጥለው መሃበሩን ሁለታኛ ቆንጽላ ጺፈት ቤት ለማዲረግ ካልሆነ ፊርኪስኪሱን ለማውጣት ተግቶ እየሰራ ይገኛል።  ድሮ ሰው ስማርና ስመራመር ለሃገር ዋልታና ማገር ይሆናል በአሁን ሰዓት ግን ወያኔ በራሱ ልክ ሰፊቶ የምያስተምራቸው ተማርዎቹ እንደ ዕንቦጭ አረም የሚለመልመዉን የሚያምረዉን ሁሉ ማጥፋት ስራቸው አደርገዉታል።ይህን ግዜ መማሩስ ምን ይተጠቅማል ብለን ልንጠይቅ አንችላለን። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደዚህ ቢሎ ይመክረናል ተወዳጆች ሆይ፦ ጥበባችሁ ለሥጋችሁም ለነፍሳችሁም የሚጠቅም እንጂ በዚህ ዓለምም ይኹን በሚመጣው ዓለም የሚጎዳችሁ አይኹን፡፡  ነገር ግን የወያኔ ተላላክ ምሁራኖች ዛሬን መኖር እንጅ ነገን ማሰብ ያልፈጠረባቸው ዱኩማን የተማሩትን ትምህርት ለተንኮል እና ለጉዳት ይጠቀሙታል። የሰማያዊ እሳቤያቸውን ከአፈቸው እንጂ ከልባቸው መንግለው ጥለዉታል። አንዳንዴ ሳስባቸው ወያኔ ሆይ በደደቢት የምትኖር ብለዉ ልማታዊ ጸሎት ሁላ የሚያደርጉ ይመስሉኛል። አሁን ጥያቄው በተለያየ አለም ላይ የምትኖሩ ኦርቶዶክስ ክርሲቲያኖች መሃበሩን የመታደግ ሃላፊነት አለባችሁ። ወያኔ መሃበሩን የደደቢት ክፊለ ጦር ለማድረግ የቀራት ጊዜ በጣም አጭር ነው። ስራ አስፈጻሚው ኮሚቴ ዉስጥ ህዝበ ክርስትያኑ ሳይመርጣቸው በራሳቸው ስልጣን ዋያኔዉያንን የሰገሰጉት ሳያንስ የማሃበር ደንብ አዘጋጅተናል በሚል ሺፋን ገና ህዝበ ክርስትያኑ ያልተወያየበተን ደንብ የስራ አስፈጻሚው ኮሚቴ በራሱ አጽድቁዋል በማለት  መሃበሩን ከመጀመሪያው የመሰረቱትን ነባር ኮሚቴ አባላት በማሰናበት በቁዋምነት የወያኔ አባላተን በመመደብ አስከዛሬ የተሰበሰበውን ገንዘብ እጃቸው ለማስገባትና ሃገር ቤት ልማት ይከናወንበታል በሚል ሰበብ ገንዘቡን የዉሃ ሽታ ለማድርግ ዝግጅታቸዉን ጨርሰው እነሱ እንደምሉት የይስሙላ ምርጫ ለማድረግ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።
ንቁ መሃበሩን እንታደግ።
የ እግዚሃብሄር ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን።

No comments:

Post a Comment