Sunday, August 6, 2017

በባህርዳር ሁለት የቦምብ ፍንዳታ ደረሰ | ከተማዋ በአጋዚ ወታደሮች ተወራለች



Filed unde     


File Photo
(ዘ-ሐበሻ) በአምባገነኑ ሕወሓት መራሹ መንግስት ባለፈው ዓመት ነሐሴ 1,2008 ዓ.ም የተገደሉትን ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎች ለማሰብ በባህርዳር ነገ ሰኞ የቤት ያለመውጣት አድማ የተጠራ ሲሆን በከተማዋ ዛሬ ሁለት ቦምብ መፈንዳቱን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገለጹ::
እንደዘ-ሐበሻ ምንጮች ገለጻ የቦምብ ፍንዳታው የተፈጸመው በባህርዳር በተለምዶው 11 ቀበሌ ብ አዴን ጽህፈት አቅራቢያ እና ፔዳ መስመር በሚባል አካባቢ ነው::
ለሁለቱ ቦምብ ፍንዳታዎች ኃላፊነቱን የወሰደ አካል ባይኖርም በባህርዳር በአሁኑ ወቅት ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገ መሆኑንና ከተማዋም በወታደሮች መከበቧ ታውቋል::
ባህርዳር ነገ ሰኞ ሕዝቡ አድማውን በተሳካ ሁኔታ ያከናውናል ተብሎ ይጠበቃል::

No comments:

Post a Comment