(ኢሳት ዜና ነሃሴ 9 ቀን 2009 ዓም)

ከዚህ በፊት የህገ ወጥ መሳሪያዎች ቁጥጥር ቢመደረግበት ጊዜ ለከተማ ነዋሪዎች የተከለከሉ አውቶማቲክ ጠመንጃዎች ከበርካታ ጥይቶች ጋር በእነዚሁ የህወሃት ደጋፊ ወገኖች እጅ ቢያዙም፣ በአካባቢው ከሚገኘው መኮድ እየተባለ ከሚጠራው የመከላከያ ካምፕ የሚመጡ ወታደራዊ አዛዦች የሚያዙትን ጠመንጃዎች ለስራ ተብለው የተሰጡ የመንግስት መሳሪያዎች መሆናቸውን እየገለጹ መሳሪያዎቹ ለባለቤቶቹ እንዲመለሱ ሲያደርጉ ቆይተዋል። የክልሉ ፖሊስ ይህንን ድረጊት ጠንቅቆ ቢያውቅም እርምጃ ለመውሰድ ሲደፍር አልታየም።
የአሁኑ የልዩ ጥበቃ ጥያቄ ህወሃት፣ በጸጥታ መደፍረስ ስም ከዚህ ቀደም ሲወስዳቸው የነበሩትን ሁለቱን ህዝቦች የሚጋጩ ስራዎችን ለመስራት ማቀዱን እንደሚያመለክት ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ይገልጻሉ።
በተያያዘ ዜና ባለፈው እሁድ የክልሉ የመረጃ አካላት ከዞን ፖሊስ መምሪያ ሃላፊዎች ጋር ጎንደር ላይ ባደረጉት ስብሰባ፣ በአገዛዙ ላይ ስለተቃጣው አደጋና የጸጥታ መደፍረስ ተወያይተዋል። የክልሉ የደህንነት አካላት ስራቸውን በተገቢው ሁኔታ እየሰሩ አይደለም በሚል ወቀሳ ቀርቦባቸዋል። በባህርዳር ከተማ የሚደረሰውን የቦንብ ፍንዳታ ማስቆም አለመቻሉ የግምገማው ዋና አጀንዳ የሆነ ሲሆን፣ በአደባባይ እየተዛተ የሚደረገው ፍንዳታ በክልሉ ያለው ችግር ውስብስብና ሰፊ መሆኑ ተገልጿል። ኢሳት ቀደም ብሎ እንደዘገበው ፍንዳታውን አደረሱ ተብለው የተያዙ ሰዎች ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰዎች መሆኑ በስብሰባው ላይ የተወሳ ሲሆን፣ ይህም በደህንነቱ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የመረጃ ክፍተት መኖሩን ያሳያል ተብሎአል።
በአዲስ መልክ የተዋቀረው የጸጥታ ስራ ምንም ለውጥ አለማምጣቱ በስብሰባው ላይ ተደጋግሞ ተነስቷል። በክልሉ ያሉት አብዛኞቹ የደህንነት ሰራተኞች እና የፖሊስ አባላት የህወሃትን የበላይነት እየተቃወሙ እንደሆኑ የሚደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።
No comments:
Post a Comment