Thursday, August 24, 2017

የካናዳ ኢምባሲ በሐረርና ድሬደዋ እንዲሁም ከሆለታ እስከ አምቦ ዜጎቹ እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈ


       




አወዳይ ከተማ ለ2ኛ ቀን ዝግ ናት
(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተጀመረው የአምስት ቀናት አድማ በዛሬው እለትም በተለያዩ ከተሞች ለሁለተኛ ቀን እየተካሄደ ነው:: በተለያዩ ቦታዎች የስር ዓቱ ወታደሮችና ተላላኪዎች ሱቃቸውን ያልከፈቱትን እያሸጉ እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎት ያልሰጡትን ደግሞ ታርጋቸውን እየነቀሉ ቢሆንም ውጥረቱ ተባባሰ እንጂ አልበረደም::
ይህን ተከትሎ የካናዳ ኢምባሲ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚኖሩት ዜጎቹ ባስተላለፈው ማስጠንቀቂያ ክትናንት ጀምሮ ማንኛውም የካናዳ ዜጋ ወደ ሐረርና ድሬደዋ እንዲሁም ከሆለታ እስከ አምቦ ባሉት ከተሞች እንዳይንቀሳቀሱ አዟል::
በኦሮሚያ ከተሞች አሁንም ውጥረቱ እንዳየለ ነው
ጉዳዩን ተከታትለን እንዘግባለን::

No comments:

Post a Comment