Tuesday, August 22, 2017

ሙስና ገንዘብ መቀበል ወይም መስረቅ ብቻ ኣይደለም ፡፡ የመንግስት ስልጣንን በዝምድና መከፋፈልም አይን ያወጣ ሙስና ነው – ብርሃን ኪሮስ


By ሳተናውAugust 22, 2017 04:13



ጉዳዩ፡ በኢትዮጵያ አየተካሄደ ስላለው ሙስና ይመለከታል

የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ወልዱን እና ባለቤቱን ወ/ሮ ትርፉ ኪዳኔን እንደ ምሳሌ ብንወስድ ለባልና ለሚስት ከፍተኛ የመንግስት ስልጣንን ያንበሳውን ድርሻ መቸር ማለት ስልጣንን ተገን ኣድርጎ መጠቃቀም ኣና ሙስናዊ ኣድሎ ኣንዳለ ያሳያል፡፡
ወ/ሮ ትርፉ ኪዳን በኣምባሳደርነት እዚህ አውስትራሊያ ተሹማ ከመጣች ሁለት ዓመት ቢሆን ነው ሆኖም ወ/ሮ ትርፉ ከተመደበችበት ስራ በላይ ትኩረት ሰጥታ የምትስራው አውስትራሊያ ነዋሪ ከሆኑ ጥቂት ኢትዮጵያን ግለሰቦች ጋር  በመመሳጠር እና ብዙ ሚሊየን ዶላር ኢንቭስት በማድርግ ሪል ስቴት ንግድ ላይ ነው ፡፡ እዚሀ አውስትራሊያ ከመምጣትዋ በፊት የዘረፈችውን እና ኣንዲሁም በባለቤትዋ  እየተዘረፈ በኢምባሲ በኩል የሚሸሸውን የሀገር ሀብት የኣምባሳደርነትዋን ሹመትዋን ተገን በማድረግ በተለያየ ኣውስትራልያ ሰቴት በሚኖሩ ሶስት ግለሰቦች ሰም ከፍተኛ ንግድ እያካሄደች ነው ያለው፡፡
ከሶስቱ ኣንዱ የሆነው ሜልበርን ከተማ የሚገኘው አቶ ኬኔዲ ገብረየሱስ የተባለው  ግለስብ  ከጥቂት ዓመት በፊት ኣንደማንኛውም የሜልበርን ነዋሪ ኢትዮጵያዊ ኖርማል ህይወት ይኖር የነበረ ነው ፡፡  በአጭር ጊዜ ውስጥ ግን በሚሊዮን ዶላር የሚገመቱ የመኖርያ ቤቶችን ኣና የንግድ መደብሮችን በመግዛት እና በመገንባት ለምሳሌ በቅርቡ ሜልበርን የሚገኘውን ዳሽን ኢትዮጵያ ሬስቱራንት ህንፃን ግዝቶ በማከራየት መጠነ ስፊ ንግድ እያካሄደ ይግኛልልላው ። አቶ ኬኔዲ ከአምባሳደርዋ ጋር በጣም ቅርበት ያለው ከመሆኑም በላይ  በየቦታው የአምባሳደርዋ ዋና አጃቢ በመሆን የሚታየው አሱ ነው፡፡
ኣንዲሁም ከአምባሳደርዋ ጋር በመመሳጠር በስፋት ቢዝነስ እያካሄደ ያለው  ሌላው የሜልበርን ነዋሪ  የሆነው አቶ ማማየ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ግለሰቦች በአንድ ጊዜ ተስፈንጥረው ወደ ሚሊየነርንት የተሸጋገሩበት ኣና የሀብታችው የእደገት ፍጥነት በጣም አስገራሚ ስለሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያውቀውን መረጃ ሜልበርን ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በመስጠት ያለ አግባብ ኣየተዘረፈ ያለውን የሀዝብ ሀብት ዝርፍያ ለማስቆም ሀገራዊ ግዴታችንን መወጣት አለበን።

No comments:

Post a Comment