Wednesday, August 23, 2017

የባህርዳር አውቶቡሶች አድማውን ተቀላቀሉ | ♦ከአማራ ክልል ወደ ኦሮምያ ክልል የሚሄድ መኪና አቁመዋል!


          
      


ሙሉነህ ዮሐንስ እንደዘገበው
ነሃሴ 16 2009 | በመላ የኦሮሞ ክልል የተጠራውን የመጓጓዣ የስራ ማቆም አድማ ጥሪ ለአማራው ክልልና ለሌሎችም መተላለፉ ይታወሳል። ይህን መሰረት አድርጎ ከባህርዳር ወደ ነቀምትና ወደ ተለያዩ ቦታወች የሚሄዱ መኪኖች ለመንገደኛች ትኬቱን መልሠዋል። አድማ ስለተጠራ መኪኖቻን ይመቱብናል ጥሪውን መሰረት አድርገን ከስራ ታቅበናል ብለዋል። ከአማራ ክልል ወደ ኦሮምያ ክልል የሚሄድ መኪና አቁመዋል። ይህ ለወያኔ እጅግ አስደንጋጭ ሲሆን ለነፃነት ናፋቂው የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ ትግሉ ሃገራዊ ገፅታው እየተሳሰረና እያደገ መምጣቱን ያረጋግጣል።

No comments:

Post a Comment